Friday, December 5, 2014

አንዱዓለምና እስክንድር ሰው ናፍቀዋል የሰው ያለህ እያሉ ነው!!!! ዛሬ

አንዱዓለም አራጌን ለማየት ቃሊቲ ጎራ ብዬ ነበር ፡፡ ቃሊት ሁለት ሰው ማየት ስለማይቻል ከአንዱዓም ጋር የተሳረውን እስክንድርን ማግኘት አልቻልኩም፡፡ አንዱዓለም እና እስክንድርን መጠየቅ የሚቻልበት ሰዓት እጅግ አጭር ከመሆኑ የተነሳ ጠያቂዎቻቸው ተሰፋ እየቆረጡ እነርሱም ሰው እየናፈቃቸው እንደሆነ ሲነግረኝ ልቤ ስብር ብላለች፡፡ ገና ከአሁኑ ጠያቂዎች ወደኋላ ማለት ከጀምርን እነዚህ ልጆች እየከፈሉ ያለውን መሰዋዕትነት ችላ ማለት ብቻ ሳይሆን ሸክሙን ሁሉ ለቤተሰቦች ጥለን ትግል ላይ ነው ያለነው ማለት አይቻልም፡፡
የህሊና እስረኞች ጉዳይ ያገባናል የሚል ሁሉ ጀግኖቻችንን መጎብኝትና ማበረታት የግድ ይላል፡፡ በቅርብ ያሉት በዚህን ያህል የሰው ናፍቆት ካደረባች እሩቅ የሚገኙት እነ ናትናኤልና ሰይፈ ሚካኤል በምን ደረጃ እንደሚገኙ
መገመት አያሰቸግርም፡፡ ከወሬ ወጥተን አለን ብንል ምን ይመስላችኋል ጎበዝ …. ዘወትር ከአምስት እሰከ ስድስት ሰዓት የመጠየቂያ ሰዓት መሆኑን ማስተወስ ተገቢ መሰለኝ፡፡
በዚሁ አጋጣሚ እነ ሀጎስ ያለምንም ማጉላላት ከአንዱዓለም ጋር ተገናኝቼ ለ45 ደቂቃ እንድናወጋ በማድረጋቸው ምስጋናዬ ይድረሳችሁ፡፡ እስረኛ መጠየቅ ህገ መንግስታዊ መብት መሆኑን ዘንግቼው ሳይሆን ስታንገላቱኝ መውቀስ ብቻ እንዳይሆን ብዬ ነው፡፡


No comments:

Post a Comment