Thursday, December 11, 2014

ደህንነቶች እስረኞችን ነጣጥለው እያዋከቡ ነው

የገዥው ፓርቲ ደህንነቶች የአዲስ አበባ ፖሊስ ጣቢያ (ሶስተኛ) የሚገኙትን የተወሰኑ እስረኞች ‹‹አብራችሁን ካልሰራችሁ አንለቃችሁም!›› እያሉ እያዋከቡ ነው፡፡ ሶስተኛ ታስረው ከሚገኙት መካከል ሳሙኤል አበበ፣ ምኞት መኮንን፣ ሜሮን አለማየሁና መርከቡ ሀይሌ ውጭ ሌሎቹ የመታወቂያ ዋስ አምጥተው እንዲለቀቁ የተጠየቁ ሲሆን አራቱን እስረኞች ‹‹አንራችሁን ካልሰራችሁ አንለቃችሁም!›› እያሉ እያዋከቧቸው መሆኑን ለማወቅ ተችሏል፡፡

በተመሳሳይ ፖፖላሬ እስር ቤት ከሚገኙት መካከል ዮናስ ከድርንና ተስፋዬ መርኔን ደህንነቶች ‹‹የእናንተን ምርመራ አልጨረስንም፡፡ ትቆያላችሁ!›› እንዳሏቸው ተገልጾአል፡፡


No comments:

Post a Comment