Monday, December 22, 2014

ኢሳት ዜና 





ኢሳት ዜና :-የደቡብሱዳንፕሬዝደንትሳልቫኪርባለፈውአርብ  አዲስአበባውስጥከተቀናቃኛቸውዶ/ርሪክማቻርጋርየሰላምስምምነቱንየፈረሙትጠቅላይሚኒስትርኃይለማርያም “አስርሃለሁ” ብለውስላስፈራሩኝነውሲሉየተናገሩት “ለቀልድነው” ሲልየኢትዮጵያመንግስትመግለጹን ሰንደቅ ዘግቧል።
ሳልቫኪርከተቀናቃኛቸውዶርሪክማቻርጋርየሰላምስምምነትፈርመውወደሀገራቸውእንደተመለሱጁባየአየርማረፊያተሰብስበውለሚጠብቋቸውሰዎችበሰጡትመግለጫየኢትዮጵያውጠቅላይሚኒስትርኃይለማርያምደሳለኝእሳቸውንምሆነተቀናቃኛቸውንየሰላምስምምነቱንሳይፈርሙከአዲስአበባንቅንቅእንደማይሉእንዳስጠነቀቋቸውተናግረው ነበር።
አቶሀይለማርያምዶ/ርማቻርንባናገሩበትዕለትጠዋትእሳቸውንም፦ “ይሄንንስምምነትካልፈረምክአስርሃለሁ” እንዳሏቸውየጠቀሱትሳልቫኪር፤ እሳቸውምበምላሻቸው “በዚህችጥሩሀገርእኔንካሰርከኝእርግጠኛነኝጥሩምግብይቀርብልኛል።ስለዚህወደጁባመመለስአያስፈልገኝም።በነፃምትመግበኛለህ” ብለውመመለሳቸውንነውየገለጹት።
ይህየሳልቫኪርመግለጫብዙዎችንያስገረመሲሆን፤የኬንያውንደይሊኔሽንንጨምርበበርካታሚዲያዎችሽፋንአግኝቷል።ነገሩማነጋገሩንበቀጠለበትበአሁኑወቅትሰንደቅሳምንታዊጋዜጣስለጉዳዩጥያቄያቀረበላቸውየጠቅላይሚኒስትርሀይለማርያምደሳለኝቃልአቀባይአቶጌታቸውረዳ፤<< ፕሬዝዳንቱይሄንንቃልየተናገሩትየሰላምስምምነቱንበማስፈራራትናበጫናመፈረማቸውንለማመልከትሳይሆንለቀልድሲሉ  ነው>> በማለት ምላሽሰጥተዋል።
<<የፕሬዝዳንቱአነጋገርየሰላምስምምነቱንአስፈላጊነትበተመለከተያላቸውንቁርጠኝነትለመግለፅእንጂንግግራቸውስምምነቱንበግዴታየተፈፀመለማስመሰልአይደለም፤ሆኖምሚዲያዎችግንሁኔታውንአሉታዊበሆነመንገድማራገባቸውየተለመደነው፤ኢትዮጵያሁለቱንተቀናቃኝወገኖችየሰላምንአቅጣጫእንዲከተሉጥረቷንትቀጥላለች።የእነሱሰላምየእኛምሰላምመሆኑንበመረዳትበተሟላመልኩተሳትፎአችንንእንቀጥላለን>> ሲሉምአቶጌታቸውአክለዋል።




ፕሬዚዳንትሳልቫኪር እስካሁን ድረስ “ለቀልድስልየተናገርኩትነው>> በማለት ማስተባበያ አልሰጡም።

No comments:

Post a Comment