Tuesday, September 9, 2014

በአዲስ አበባ በየሰፈሩ ዲሽ የሚገጥሙ ወጣቶች “ኢሳትን እየቀጠላችሁ ነው በሚል ወከባ ይደርስባናል” አሉ

አዲስ አበባ ውስጥ በየ ቤቱ እየዞሩ ዲሽ የሚገጥሙ ወጣቶች ‹‹ኢሳትን እየቀጠላችሁ ነው›› በሚል ወከባ እንደሚደርስባቸው ገለጹ፡፡ ወጣቶቹ ከኢሳት ውጭ ያሉ ጣቢያዎች የሚተላለፉበት ዲሽ በሚገጥሙበት ወቅትም ‹‹ኢሳትን እየቀጠላችሁ ነው፡፡ ህዝቡ ኢሳትን እንዲያይ ታደርጋላችሁ›› በሚል በደህንነቶች ወከባ እንደሚደርስባቸው ለነገረ ኢትዮጵያ ተናግረዋል፡፡

በተመሳሳይ ከወራት በፊት መርካቶ አካባቢ ዲሽ የሚገጥሙ ወጣቶች ‹‹ኢሳትን ለህዝቡ እያሳያችሁ ነው›› ተብለው በፖሊስ ተይዘው እንደነበር ተጠቁሟል፡፡ ያም ሆኖ ግን በተለያዩ የአዲስ አበባ አካባቢዎች ኢሳትን እንደሚገጥሙ የሚያሳዩ የዲሽ ማስታወቂያዎች ይታያሉ፡፡ ምንጭ ነገረ ኢትዮጵያ


No comments:

Post a Comment