Saturday, September 6, 2014

የኢህአዴግ አባላት በድርጅታቸው ላይ ጥያቄዎችን ማንሳት ቀጥለዋል

በአዲስ አበባ በተለያዩ ክፍለከተሞች በመካሄድ ላይ ባለው የኢህአዴግ አባላት ስብሰባ ፣ አባላቱ ዛሬም በርካታ ጥያቄዎችን ሲጠይቁ መዋላቸውን ከውስጥ ምንጮች የተገኘው መረጃ ያመለክታል።

ዛሬ ከሰዓት በኋላ በአባላቱ ከተነሱት ጥያቄዎች መካከል፡- ” የኢትዮጵና የኤርትራ ህዝቦች የማይነጣጠሉ የአንድ ሃገር ዜጎች ሆነው ሳለ በመሪዎች አለመግባባትና ሽኩቻ በመለያየታቸው እስከዛሬ ድረስ እየተላቀሱ ይገኛሉ፤ ይህም የሆነው በኢህአዴግም አስተዋፆ ጭምር ነው፤ አሁንም ቢሆን ከኛ ጋር መስማማት ከፈለጉ በራችን ክፍት ነው የምትሉት ከልባችሁ ነወይ?” የሚለው ጥያቄ ሰፊ ሰአት ወስዶ ማከራከሩ ታውቋል።
በሃይማት አክራሪነት ጉዳይ ለተነሱት ጥያቄዎች ደግሞ ” ሰማያዊ ፓርቲ በአዲስ አበባ ሰልፍ በጠራበት ጊዜ ሰልፈኛው መስኪድ አካባቢ ሲደርስ ሙሉ ለሙሉ ለጸሎት ወደ መስኪድ እንደገባ አረጋግጠናል፤ ስለሆነም
” መንግስት ሁሉንም ሚዲያዎች እንደጥፋተኛ ቆጥሮ ጋዜጦችና መጽሔቶችን እንዳለ ከገበያ ማስወጣቱ እኛ አባሎቹ የኢህአዴግን ክፍተት የምናውቅበት መንገድ ተዘግቷል፤ ኢህአዴግ ለስራ አጥ ዜጎች የስራ ዕድል እፈጥራለሁ እያለ በአንፃሩ ግን የስራ ዕድል የሚፈጠርላቸው ዜጎች በአባልነት ላይ የተመረኮዘ ለምን ይሆናል? በታችኛው ህብረተሰብ አካባቢ በብልሹ አሰራር ውስጥ ገብተው ከፍተኛ ሙስና የሰሩና በህዝቡ የተገለሉ ሰዎች ተሸፍነው ወደ ላይ ሲወጡ ሹመት ይደረብላቸዋል ይህ ተገቢ ነወይ?” የሚሉ ጥያቄዎችም ተነስተዋል።
የአዲስ አበባ የመሬት ወረራ ጉዳይም ሰፊ አጀንዳ የነበረ ሲሆን፣ ኢህአዴግ በሰላማዊና ጠንካራ ተቃዋሚዎች ላይ የያዘው አቋምም ትችት አዘል ጥያቄ አስነስቶበታል።

የዛሬውን የፕላዝማ ውይይት የአዲስ አበባ ምክትል ከንቲባ አቶ አባተ ስጦታው መርተውታል።
ትናንት ከሰአት በሁዋላ በነበረው የውይይት ጊዜ ደግሞ ” ኢህአዴግ ለሃገሪቱ ስጋት ብሎ ከለያቸው የፖለቲካ ጉዳዮች ውስጥ ዋነኛ ያላቸው የሃይማኖት አክራሪነት ወይም ጽንፈኝነት እና የመልካም አስተዳደር እጦት ቢሆኑም፣ የ ኑሮ ውድነቱ በስጋትነት ሊካተት ይገባል” የሚል አስተያየት ቀርቧል።
የደመወዝ ጭማሪው አርኪ አለመሆኑና እንዳውም የበለጠ ህዝቡንና የመንግስት ሰራተኛውን ለችግር መዳረጉም በአባላቱ ተነስቷል።
ሰልጣኞቹን በሚሰለጥኑበት ቦታ ጥያቄዎች ሲነሱ እዚያው በህዋሳቸው በሰልጣኞቹ እንዲመለስ በማሰብ በህዋስ ማደራጀት መጀመሩን፣ ሰልጣኞቹ የመድረኩን የፕሮፓጋንዳ ገለፃ ብዙ ትኩረት ሳይሰጡ የጥያቄና መልስ ክፍለ ጊዜ ሲደርስ ግን በንቃት ጥያቄ የሚያነሱ ሲሆን፣ አንዳንዳ ጥያቄዎችን ከውይይሩ ጋር ግንኙነት የላቸውም ወይም ጥያቄውን ወደ ኋላ ላይ ማንሳት ትችላላችሁ በሚል እንደሚታለፉ የውስጥ ምንጮች ገልጸዋል።
ዘግይቶ በደረሰን ዜና ደግሞ የግንቦት 7 ድርጅት አጀንዳ የነበረ ሲሆን በአንዳንድ አባላት ዘንድ ግንቦት 7 ከውጭ መንግስታት ጋር በማበር በሀገር አብዮት እንዲነሳ እየሰራ ነው ሲሉ ሌሎች አባላት ደግሞ ግንቦት 7 አሸባሪ ከተባለ ለምን የአሜሪካ መንግስት አሳልፎ አይሰጥም? እናንተ እንደምትሉት አሸባሪ ቢሆን ኖሮ ያስሩዋቸው ነበር ብለው ተከራክረዋል፡፡ አወያዮቹም ከአሸባሪዎች ጋር መገናኘት የለባችሁም፣በሀገር የሚንቀሳቀሱ ተቃዋሚዎች አብረው እየሰሩ እንደሆነ ለአባላቱ የገለጹ ሲሆን ንክኪ እንዳይኖራችሁ ሲሉ አስጠንቅቀዋል፡፡
በኢህአዴግ ታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ የታየው ግምገማ መነሻ፣ በቅርቡ ኢህአዴግ መዳከሙን የተመለከተ ግምገማ ከተደረሰ በሁዋላ ነው። ይህን ተከትሎ ለዩኒቨርስቲ ተማሪዎች፣ ፖሊሶች፣ የህግ ባለሙያዎች በመንግስት ፖሊሲ ዙሪያ ስልጠና ሲሰጥ ቆይቷል። በስልጠናው ላይ የተነሱትን ጥያቄዎች የኢህአዴግ አባላት እንዲመክቷቸው በሚል እየተሰጠ ያለው ስልጠና ያልተጠበቁ ጥያቄዎችን ማስነሳቱ፣ ከፍተኛ አመራሮችን ሳይቀር በእጅጉ ማስገረሙን ምንጮች አክለው ገልጸዋል።
“እዚህ የምናደርገው ስብሰባ በኢሳት ይዘገባል ይህ እንዴት ሊሆን ቻለ ? ” በሚል አመራሩ እየተነጋገረበት መሆኑንም ታውቋል።
ብአዴንም መረጃዎች እየወጡ ተቸግረናል በሚል ትናንት በጀመረው ግምገማ ማንም ሰው ሞባይል ስልኮችን ይዞ እንዳይገባ ከልክሏል።


No comments:

Post a Comment