Thursday, September 4, 2014

ጋዜጠኛ ታዲዮስ ጌታሁንም ተሰደደ

የሎሚ መጽሔት ማኔጂንግ ኤዲተር ጋዜጠኛ ታዲዮስ ጌታሁን ከሀገር ተሰደደ። ማክሰኞ ነሐሴ 21 /2006 ዓ.ም በኢትዮጵያ አየር መንገድ ለመውጣት ሲል በሀገር ውስጥ የደህንነት ኃይሎች ተይዞ ታስሮ የነበረ ሲሆን ነሐሴ 28 ቀን 2006 ዓ.ም ከሀገር መሰደዱ ተረጋግጧል።
መንግስት የግሉ ፕሬስ ጋዜጠኞችን በከፍተኛ ሁኔታ እያሳደደ ባለበት በአሁኑ ወቅት የሎሚ ፣የጃኖ ፣የአዲስ ጉዳይ፣የእንቁና የአፍሮ ታይምስ አሳታሚዎችን ጨምሮ አንድ ወር ባልሞላ ጊዜ ውስጥ 15 ጋዜጠኞች ከሀገር ተሰደዋል ።


No comments:

Post a Comment