Monday, November 27, 2017

አንድ በቱርክ የኢትዮጵያ ኢምባሲ ሰራተኛ “በቱርክና ኢትዮጵያ መሃል” ጦርነት ይቀሰቀሳል በማለቱ የአገሪቱ ጋዜጦች መሳለቂያ ሆነ

(ኢሳት ዜና ህዳር 18 ቀን 2010 ዓም)
ቲ ኤች በሚል ቅጽል ስም የተጠራው የኢምባሲው ሰራተኛ አክራ ውስጥ በስካር መንፈስ ውስጥ ሲያሽከረክር አንድ ታክሲ በመግጨት ጉዳት ያደረሰ ሲሆን፣ ፖሊሶች ግለሰቡ የአልኮል ምርመራ እንዲያደርግ ሲያዝዙት፣ “ እኔ የኢትዮጵያ መንግስት ተወካይ ነኝ፣ ምርመራ አላደረግም፣ በኢትዮጵያና ቱርክ መካከል ጦርነት እንዲነሳ አደርጋለሁ” በማለቱ የቱርክ የመገናኝ ብዙሃን እየተቀባበሉ ተሳልቀውበታል።
ግለሰቡ ራሱን እንደአምባሳደር ቆጥሮ በስካር መንፈስ ውስጥ ሆኖ ይናገር እንደነበር ጋዜጠኞች የዘገቡ ሲሆን በተለይ፣ ከነካችሁኝ “በኢትዮጵያና ቱርክ መካከል ጦርነት ይነሳል የሚለው አነጋገሩ” እንዳስገረማቸው ጽፈዋል።

No comments:

Post a Comment