Wednesday, October 22, 2014

ሰበር ዜና፣ ህውሃት “የመለስ ትሩፋቶች” መጽሃፍን ለስለላ እየተጠቀመበት መሆኑ ታወቀ

በቀድሞው የመንግስት ኮሚውንከሽን ጉዳዮች ሚንስትር ድኤታ አቶ ኤርምያስ ለገሰ የተጻፈውን እና በብዙ በአለም ላይ የሚገኙ ኢትዮጵያውያን ተነባቢ የሆነው “የመለስ ትሩፋቶች” የተስኘው መጽሃፍ የኢህአዴግን መንግስት በተለይም ደግሞ የህውሃትን የጥፋት ዘመቻ በሰፊው  ያጋለጠ መሆኑ ይታወቃል። ስለሆነም መጽሃፉ ወደ PDF File  ተቀይሮ በተለይ በኢትዮጵያ ውስጥ በኢሜይል ሲሰራጭ ቆይቷል። መጽሃፉ በተለይ በዲሞክራሲ አክቲቪስቶች ዘንድ ተፈለኣጊነት እንደሚኖረው በማወቅኢትዮጵያ ውስጥ ያሉ የደህንነት ምንጮቻችን በዛሬው እለት እንዳስረዱን የህውሃት ኢህአዴግ የስለላ ማእከል ይህንን ፋይል ፊን ፊሸር ከተባለ የስለላ ቫይረስ ጋር በማጣመር በአሁኑ ሰአት በከፍተኛ ፍጥነት በኢሜይል በማሰራጨት ላይ ይገኛል።ይህ ቫይረስ ከ“የመለስ ትሩፋቶች” ፍይል ጋር ተጣብቆ ወደ ኮምፒውተር ዳውንሎድ ከተደረገ፣ ኮምፒውተሮት ላይ ያለውን የግል ፍይሎች ወድ ህውሃት የስለላ ማእከል ከመላክ እልፎ  የሚከተሉትን ማድረግ ይችላል፥1)  የህውሃት ይስለላ ኤጀንቶች በኮምፒውተሮት ላይ ሙሉ ለሙሉ ቁጥጥር እንዲኖራቸው ያደርጋል2)  ይህ ማለት በፈለጉት ሰዕት የኮምፒውተሮትን ካሜራ እና ማይክሮፎን በመጠቀም የግል እንቅስቃሴዎን መከታተል እንዲችሉ ያደርጋል3) በኮምፒውተሮት ላይ በኢንተርኔት  የሚስገቧቸውን እንደ ክሬዲት ካርድ እና ሶሻል ሴኵሪቲ ያሉ ሚስጥራዊ ቁጥሮችን  በቀላሉ ማግኘት ያስችላቸዋል4) በኢንተርኔት ላይ የሚጎበኟቸውን ድረ ገጾች እንዲሁም  በግልዎ የሚሳተፉባቸውን የማህበርዊ ሚድያ አካውንቶች እስከ ዩዘር ስም እና ፓስዎርዳቸው በቀላሉ ማግኘት ያስችላቸዋል5)  ከቤተሰብዎ እና ከጏደኞችዎ ጋር የሚያደርጉትን የኢሜይል እና የስካይፒ ግንኙነት በቀላሉ ማንበብ እና ማዳመጥ እንዲሁም አካውንቶቹን ሌላ ጥቅም ላይ ማዋል ያስችላቸዋል6)  በድርጅት ውስጥም ሆነ በግልዎ ለስብአዊ መብትዎ ወይም ለኢትዮጵያ ዲሞክራሲ የሚሟገቱ ከሆነ፣ እርስዎን በሃሰት ወንጅሎ ለእስር አና ለስቃይ ለመዳረገ መንገድ ይከፍትላቸዋልስለዚህ ይህ “የመለስ ትሩፋቶች” የሚል የPDF ፍይል በኢሜይል ከተላከልዎ የኢሜይል መልእክቱን ሳይከፍቱ ዲሊት በማድረግ እራስዎን ከጥቃት ያድኑ።
አባይ ሚዲያ

No comments:

Post a Comment