Tuesday, October 28, 2014

የወያኔ እና የዶ/ር ዲማ ድርድር ለምን ለህዝብ ይፋ እንዲሆን አልተፈለገም?

ቀብር ወይንስ ድርድር ? ? ? በ24 ሰአት ድምጽህን ሳታሰማ አገሪቱን ልቀቅ የሚባልበት ሁኔታ….

በቄስ ጉዲና ቱምሳ ባለቤት ወይዘሮ ጸሃይ ቶሎሳ የቀብር ስነስርአት ላይ ለመገኘት በህወሓት ተፈቅዶላቸው አዲስ አበባ የገቡት የቀድሞ የሕወሓት ባለስልጣን እና የአርባጉጉ አሰቦት እባ በደኖ ጭፍጨፋዎች ግንባር ቀደም ተሳታፊ ዶ/ር ዲማ ነገዎ የቀብሩ ስነ ስር አት እንዳለቀ በ24 ሰአት አገር ለቀው እንዲወጡ መታዘዛቸው እየሰማን ያለንበት ሁኔታ ነው ያለው።

ለድርድር አዲስ አበባ ገቡ ሲባል አይደለም ለቀብር ነው ያለው ሕወሓት የዶ/ር ዲማን ከአባዱላ እና ከሙክታር ፋይሰል አሊ ከተባሉ የሕወሓት ታዛዦች ጋር መታየታቸው ቢጠቆምም ተከታታይ ውይይቶች ለመጀመር የሕወሓትን ቅድመ ሁኔታ ካለማንገራገር ተቀብለው እያለ ውስጣቸውን ሰላም ያልተሰማቸው የሕወሓት ሰዎች ደህንነቶቻቸን ልከው በ24 ሰአት እንዲወጡ ተደርጓል ለምን ድርድሩ ለህዝብ በሚዲያ ተነግሮ በይፋ አልሆነም የሚል ጥያቄ ስለጠየቁ ወይንስ ከኦሮሚኛ ተናጋሪ ኢትዮጵያውያን ምሁራን ጋር በድብቅ ስለተገናኙ ?

Minilik Salsawi (ምንሊክ ሳልሳዊ)

- See more at: http://satenaw.com/amharic/archives/2208#sthash.Ou3uqwfE.m4eezDrs.dpuf

No comments:

Post a Comment