Thursday, October 9, 2014

የፌዴራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት 16ኛ የወንጀል ችሎት በሦስት አሳታሚ ድርጅቶች መሪዎች ላይ የእስራት ቅጣት በየነ።

የፌዴራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት 16ኛ የወንጀል ችሎት በሦስት አሳታሚ ድርጅቶች መሪዎች ላይ የእስራት ፍርድ በየነ።

የፌዴራል አቃቤ ሕግ ዩፋ ኢንተርቴይንመንትና የፕሬስ ሥራዎች ሃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር፤ ዳዲሞስ ኢንተርቴይንመንትና ሮዝ አሳታሚ ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር በተሰኙ ድርጅቶችና በዋና ስራ አስኪያጆቻቸው ፋጡማ ኑርዬ፣ አቶ ግዛዉ ታዬ ኦርዶፋና አቶ እንዳልካቸዉ አድጉ ላይ ባቀረበዉ ክስ መሰረት፤ የፌዴራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት “ጥፋተኛ” ናቸው ሲል ወስኖባቸዋል። ሶስቱም ተከሳሾች ቀደም ብሎ አገር ጥለው የኮበለሉ ሲሆን፤ የእስራት ቅጣቱ የተፈረደባቸው በሌሉበት ነው።

ዛሬ በዋለዉ ችሎት ፍርድ ቤቱ በእያንዳንዳንዱ ተከሳሽ ላይ ከ3 አመት ከ3 ወራት እስከ 3 ዓመት ከ11 ወራት የሚደርስ እስራት ፈርዷል።

የፍርድ ቤቱን ውሳኔ ተከትሎ የዳዲሞስ ኢንተርቴይንመንት እና የፕሬስ ዉጤቶች ሚዲያ ዳይሬክተር አቶ ዳንኤል ድርሻ በስልክ በሰጡን ቃል ፍርድ ቤቱ የወሰደዉ እርምጃ የጠበቅነዉ ነዉ ብለዋል። ዝርዝሩን ከዘገባዉ ያድምጡ።


No comments:

Post a Comment