Wednesday, October 15, 2014

የአሜሪካ መንግስት ኢትዮጵያ ውስጥ አዲስ አበባ አልሸባብ ጥቃት ሊያደርስ ነውና ራሳችሁን ጠብቁ ሲል አስጠነቀቀ።

የአሜሪካ መንግስት ኢትዮጵያ ውስጥ አዲስ አበባ አልሸባብ ጥቃት ሊያደርስ ነውና ራሳችሁን ጠብቁ…ዩኤስ ኢምባሲ በመቅረብ ራሳችሁን ባሉት መረጃዎች ላይ አፕዴት አድርጉ… ሲል ጥሪውን አቀረበ፡፡

በርከት ብሎ ሰው ከሚገኝባቸው አካባቢዎች፣ እንዲሁም ኢትዮጵያዊያንና ምዕራባዊያን ከሚበዙባቸው አካባቢዎች ራሳችሁንም አርቁ ሲል ያሳስባል፡፡ ኢምባሲው እንደሚለው ከአልሸባብ ደረሰኝ ያለው መልዕክት እንደሚያሳየው ቦሌ አካባቢ ኢላማው እንደሆነ ነው የገለፀው ብሏል፡፡ ሆቴሎች ባሮች ስብሰባና ወርክሾፕ ቦታዎች፣ ሱፐርማርኬትስ እና የገበያ አዳራሾችና ትልልቅ ሱቆች ኢላማ መሆናቸውንም አስገንዝቧል፡፡
ሽብሩ ሊፈፀም እንደሚችል እርግጠኛ ባንሆንም ስጋት ውስጥ ማስገባት የሚችል ደረጃ ላይ በመሆኑ ራሳችሁን ጠብቁ ይላል ኢምባሲው ባወጣው ጥሪ፡፡ እኔ ህሊና ደሞ እላላው መንግስታችንየሚያሸብረን ይበቃል፡፡ አሜሪካ ለዜጎቿ ስታስብ እኛም ለኢትዮጵያዊያን እና ሁሉም ስዎች እናስባለንና እባካችሁን ሁላችንም ኢትዮጵያዊያን ሁላችንም አፍሪካ በዚህ እመጣለው ብሎ በዚያ ነውና የሚመጣ አልሸባብ በቦሌ እመጣለው ያለ ሊያደናግር ሊሆን ስለሚችል ቦሌ እመጣለው ካለ መርካቶ ሊሆን ስለሚችል ታርጌቱ መርካቶዎችና ሌሎች አካባቢም ራሳችሁን ጠብቁ ነው መልዕክቴ፡፡
አሜሪካን ግን ታዘብኩሽ ልክስክስ ነገር ነሽ ለራስሽ ዜጋ ስታግዥ እኔም ለወገኖቼ ጥሪውን አስተላልፋለው የሚሰጎድ መሪ ብናጣም ቅሉ፡፡ ስለዚህ ሁላችሁም አዲስ አበባዎች ብቻ ሳይሆን መላው ኢትዮጵያዊያን ጥቃቱ ምናልባት የሚደርስ ከሆነ ሊደርስ ስለሚችል ራሳችሁን አንቁና ጠብቁ ምናልባትም ጥቃቱን የሚያደርሰውም ማን እንደሆነ ስላልተለየ ላለመድረሱ ምንም ዋስትና የለንምና፡፡


No comments:

Post a Comment