Friday, October 3, 2014

አንድ መምህር ጠንካራ ጥያቄዎችን ብቻ በመጠየቃቸው መታሰራቸውን ገለጹ

ኢሳት ዜና :-ኢህአዴግ ለመምህራን እየሰጠ ባለው የፖለቲካ ስልጠና ላይ የሚሳተፉት በወሊሶ ከተማ አስተማሪ የሆኑት ግለሰብ “ጠንካራ ጥያቄዎችን መጠየቃቸውን” ተከትሎ መታሰራቸውን ለኢሳት ገልጸዋል።
መምህሩ እንዳሉት ” የመንግስት ባለስልጣናት መሬት እየከፋፈሉ መሸጣቸውን አስመልክቶ ማስረጃ አቅርበው በመጠየቃቸው” ህዝብን “ልታነሳሳ ነው” በሚል ለአንድ ቀን ታስረው ” ሁለተኛ እንዳትናገር በሚል በማስጠንቀቂያ መፈታታቸውን ተናግረዋል።
ማስጠንቀቂያው ከተሰጣቸው በሁዋላ ጥያቄ መጠየቅ ማቆማቸውንም አክለው ገልጸዋል


No comments:

Post a Comment