Wednesday, September 14, 2016

በኮንሶ በርካታ ዜጎች ተገደሉ : አካባቢው የጦርነት ቀጣና ሆኗል ተባለ

መስከረም ፬ (አራት) ቀን ፳፻፱ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-
የመከላከያ ሰራዊት እና የደቡብ ክልል የልዩ ሃይል አባላት በኮንሶ ህዝብ ላይ እየፈጸሙት ባለው ጥቃት በርካታ ዜጎች ተገድለዋል። እስካሁን ድረስ ባለው መረጃ ከ25 ያላነሱ ሰዎች ተገድለዋል። የአካባቢው ነዋሪዎች ግን የሟቾች ቁጥር ከዚህም በላይ ይሆናል ይላሉ። ከተገደሉት መካከል አንድ አራስ ሴት በጥይት ተደብድባ ስትገደል፣ ህጻኑ በወታደሮች ተወስዷል በማለት የአገር ሽማግሌዎች ገልጸዋል።
ትናንት ብቻ ከ4 ሺ 50 በላይ ሰዎች የተሰደዱ ሲሆን፣ ዛሬም ስደቱ ቀጥሎአል በማለት የአገር ሽማግሌዎች ይናገራሉ።
ጭፍጨፋውና እልቂቱ ሊቀጥል እንደሚችል የአገር ሽማግሌዎች ስጋታቸውን ገልጸዋል።

No comments:

Post a Comment