Wednesday, September 28, 2016

ኢትዮጵያ የኢኮኖሚ ነጻነት ከሌለባቸው አገራት አንዷ ናት ሲል አንድ አለም አቀፍ ተቋም ይፋ አደረገ

ኢሳት (መስከረም 17 ፥ 2009)

ኢትዮጵያ ኢኮኖሚያዊ ነጻነት የሌለባቸው ሃገራት ተብለው ከተፈረጁ የአለማችን ሃገራት መካከል አንዷ ሆና መገኘቷን አንድ አለም አቀፍ የፋይናንስ ተቋም ይፋ አደረገ።
ከ90 ሚሊዮን ህዝብ በላይ ያላት ሃገሪቱ ላለፉት 10 አመታት ኢኮኖሚያዊ ዕድገትን አስመዝግባለች ተብላ ቢነገርላትም፣ ኢኮኖሚያዋ በአብዛኛው ነጻ ያልሆነ ሆኖ በጥናት መገኘቱ በ186 ሃገራት ላይ ያካሄደውን የጥናት ግኝት በህዝብ ያቀረበው ሄሪቴጅ ፋውንዴሽን የተሰኘ ተቋም አስታውቋል።
በነፍስ ወከፍ 250 ካሬ እየተሰጣቸው ለዘመናት ከኖሩበት የእርሻ ቦታ እንዲነሱ የተጠየቁ አርሶ አደሮች የቀረበላቸው ተለዋጭ ቦታ ለኑሮ ምቹ አለመሆኑን በመግለጽ ተቃውሞ በማቅረብ ላይ መሆናቸውን በሃገር ውስጥ ያሉ መገናኛ ብዙሃን ዘግበዋል።
ተለዋጭ ቦታው ለልማትም ሆነ ለማህበራዊ ህይወታቸው አመቺ አለመሆኑን በመግለፅ ላይ ያሉት አርሶ አደሮች የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ሊሰጣቸው ባሰበው ምትክ ቦታና ካሳ ላይ ማስተካከያን እንዲያደርግ ጠይቀዋል።

ባለፈው ሃምሌ ወር በዚህ ክፍለ ከተማ አካባቢ ህወሃት የተባሉ የመኖሪያ ቤቶችን ለማፍረስ በተካሄደ ዘመቻ አርሶ አደሮችና ነዋሪዎች ከጸጥታ ሃይሎች ጋር መጋጨታቸው ይታወሳል። ሁለት የጸጥታ አባላትና አንድ የክፍለ ከተማ ስራ አስፈጻሚ መገደላቸውን እማኞች በወቅቱ ለኢሳት አስረድተዋል።
የከተማዋ አስተዳደር አዲስ አበባ ከተማን ወደ ኦሮሚያ ክልል ለማስፋፋት የያዘውን እቅድ ተቃውሞ መቀስቀሱን ተከትሎ በአዲስ አበባ ዙሪያ መሬትን የተጠየቁ የውጭ ባለሃብቶች ከከተማዋ ዳርቻ ቦታ እየተሰጣቸው መሆኑ ይነገራ።
በኦሮሚያ ክልል የተቀሰቀሰውን ህዝባዊ ተቃውሞ ተከትሎ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በከተማዋ ዙሪያ ያሉ የእርሻ ቦታዎችን ለውጭ ባለሃብቶች ለመስጠት የያዘውን ዕቅድ መሰረዙ ይታወሳል።
ይሁንና የዕቅዱ አለመሳካትን ምክንያት በማድረግ አስተዳደሩ በአዲስ አበባ ዳርቻ ባሉ ቦታዎች ቃል ለገባው የመሬት አቅርቦት ምላሽን ለመስጠት ጥረት እያደረገ መሆኑን ለጉዳዩ ቅርበት ያላቸው አካላት ይገልጻሉ።
ከሶስት ወር በፊት በቦሌ ክፍለ ከተማ ቦሌ አውሮፕላን ማረፊያ ዙሪያ ህገወጥ የተባሉ የመኖሪያ ቤቶችን ለማፍረስ በተካሄደ ዘመቻ ግጭት ተቀስቅሶ ከ10 የሚበልጡ ሰዎች መሞታቸው የሚታወስ ነው።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ህገወጥ የተባሉ የመኖሪያ ቤቶችን የማፍረሱ ሄደት በተያዘው አመት ተጠናክሮ እንደሚቀጥል በቅርቡ ባካሄደው የካቢኔ ልዩ ጉባዔ ውሳኔን አስተላልፏል።
በኦሮሚያ ክልል ከወራት በፊት የተቀሰቀሰውን ህዝባዊ ተቃውሞ ተከትሎ ነዋሪዎች አርሶ አደሮችን ያለ አግባብ ከይዞታቸው የማፈናቀሉ ድርጊት እንዲቆምና የሰብዓዊ መብት እንዲከበር ጥያቄን ሲያቀርቡ መቆየታቸው ይታወሳል።
ሂውማን ራይትስ ዎች ጨምሮ በርካታ አለም አቀፍ የስብዓዊ መብት ተሟጋች ድርጅቶች በኦሮሚያ ክልል ብቻ ከ500 የሚበልጡ ሰዎች በመንግስት የጸጥታ ሃይሎች መገደላቸውን በተደጋጋሚ ሲገልጹ ቆይተዋል።
ይኸው ህዝባዊ ተቃውሞ አለም አቀፍ ትኩረት ማግኘቱን ተከትሎ አሜሪካና የአውሮፓ ህብረት ግድያውን በመኮነን ድርጊቱ በአለም አቀፉ ገለልተኛ ቡድን አካል ምርመራ እንዲካሄድበት ጥሪን አቅርበዋል።
ይሁንና የኢትዮጵያ መንግስት ለቀረበው ጥያቄ ተባባሪ እንደማይሆን በመግለጽ የራሱን ማጣራት እንደሚያካሄድ ምላሽን ቢሰጥም፣ ግድያውንና የሰብዓዊ መብት ጥሰቱን በየትኛው አካልና መቼ እንደሚያካሄድ ግን የሰጠው መረጃ የለም።

No comments:

Post a Comment