Monday, September 12, 2016

ህዝቡ የስልጣን ባለቤት አለመሆኑ አገሪቷን ለችግር እንደዳረጋት የሙስሊም የመፍትሄ አፈላላጊ ኮሚቴ ገለጸ

ኢሳት (መስከረም 2 ፥ 2009)
የሙስሊም የመፍትሄ አፈላላጊ ኮሚቴ በኢትዮጵያ የህዝብ ስልጣን ባለቤትነት አለመከበር እንዲሁም የዕኩልነትና የእኩል ተጠቃሚነት መርህ አለመተግባርና ዜጎችን ሁሉ ሊያሳትፍ የሚችል ዴሞክራሲያዊ ስርዓት እጦት ሃገሪቱ በአሁኑ ወቅት ላለችበት አሳሳቢ ሁኔታ መንስዔ መሆኑን ገልጿል። 
በመካሄድ ላይ ያለው ህዝባዊ ተቃውሞ ለአመታት የተከማቸ የህዝብ ብሶት ውጤት ነው ያለው ኮሚቴው፣ በስልጣን ላይ ያለው ገዢው መንግስት ለዘመናት የህዝብን ጥያቄን ሲያጣጥል ቆይቷል በማለት ባወጣው መግለጫ አመልክቷል። 
በአማራና ኦሮሚያ ክልሎች ለተገደሉ ሰዎች ሃዘኑን የገለጸው ኮሚቴው በህዝብ ዘንድ የተነሱ ጥያቄዎችን ተገቢ ምላሽ ማግኘት እንዳለባቸው በወቅታዊ የሃገሪቱ ጉዳዮች ዙሪያ ባወጣው መገለጫ አስፍሯል።

No comments:

Post a Comment