Wednesday, September 14, 2016

መምህራን በእያመቱ በሚጠራው የገዢው ፓርቲ ስብሰባ መሰላቸታቸውን ገለጹ

መስከረም ፬ (አራት) ቀን ፳፻፱ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-
ገዢው ፓርቲ በመላ አገሪቱ የተነሳበትን ህዝባዊ ተቃውሞ ለማብረድ በሚል ትምህርት የሚጀመርበትን ጊዜ በማራዘም መምህራንን ለ2 ሳምንት የሚቆይ ስብሰባ የጠራ ሲሆን፣ በዛሬው ስብሰባ መምህራን በእያመቱ በሚደረገው አንድ አይነት ውይይት መሰላቸታቸውን ገልጸዋል።
“መምህራኑ ከትምህርት ጋር ባልተያያዘ ጉዳይ ለምን እንሰበሰባለን?” የሚል ጥያቄ ቢያቀርቡም፣ ግዴታ መሆኑ ተነግሯቸዋል።
መምህራኑ የጧቱን ዝግጅት ተካፍለው የከሰአቱን አብዛኞቹ አለመሳተፋቸውን መምህራን ተናግረዋል

No comments:

Post a Comment