Friday, May 15, 2015

የኢትዮጵያ ብሮድካሲቲንግ ኮርፖሬሽን ለቴሌቪዥን ስርጭቱ ገንዘብ ለመሰብሰብ በተንቀሰሳቀሰባቸው ከተሞችህዝቡ የቴሌቪዥን ግብር አንከፈልም ሲል ተቃውሞውን እየገለጸ ነው

ሚያዝያ ፯ (ሰባት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- የኢትዮጵያ ቴሌቪዥን ተጠናክሮ በደረሰው ሪፖረት ህዝቡ “እኛ ኢቲቪን (ኢቢሲን) አይተን አናውቅም ፤ ለውሸት ጣቢያ ፈፅሞ ክፍያ አንፈፅምም ፤ በአይናችን ያየነውን ለሚክድ ሚዲያ
እኛ ምንም ድጋፍ አናደርግም፡፡ እንደዚህ የሚባል ጣቢያ አለ እንዴ ፤ ኢቲቪ የሚባል ጣቢያ መኖሩን አናውቅም ነበር ” የሚሉ አስተያየቶች ሲሰጡ፣ አንዳንዶች ደግሞ “እኛ ከኢሳት ውጭ ምንም ጣቢያ ሰምተንም አይተንም አናውቅም ፣
ሶሰት አመታት አለፈን” የሚሉ አሰተያየቶች ሰጥተዋል።
ኢቲቪ በሀገሪቱ ያለውን የቴሌቪዥን ቁጥር ወደ ግብር ሰንሰለት ለማሰገባት ያደረገው ጥረትም እንደከሸፈበት በሙሉ ሪፖርቱ ተካቷል፡
አየር ላይ ያለሰሚ እና ተመልካች ከሚባክኑ ጣቢያዎች መሃከል አንዱ ነው የሚለው ሪፖርቱ፣ የኢሳትን መረጃ የሚጋፋ ሚዛን መያዝ እንደማይቻል ያትታል፡፡
ሀዝቡ ኢሳት ቴሌቪዥንን ለማገዝ ከፍተኛ መነሳሳት እንዳሳየ በዚሁ አጋጣሚ ከተሰበሰበው የዳሰሳ ጥናት ሪፖርት ለማወቅ ተችሏል፡፡
የኢቲቪን ( ኢቢሲን) ግብር ለመሰብሰብ ከውሃ ፤ ከቴሌ እና ከመብራት ደረሰኝ ክፍያ ጋር ማቀናጀት እና አዲስ በሚገዙት ላይ የቴሌቪዥን ሽያጭ መደብሮች የውክልና ምዝገባ እንዲያ
ካሂዱ መስጠት እንደሚያስፈልግ የሚጠቁም የመፍትሄ ሀሳቦች በጥናቱ ተካተዋል ፡፡ የኢትዩጵያ ቴሌቪዥን በህዝብ በጀት የሚተዳደር ሲሆን በአመት እስከ 123 ሚልዩን ብር ከማስታወቂያ የሚሰበሰብ ተቋም ነው፡፡
በሌላ ዜና ደግሞ ኢሳት ስርጭቱን እንደገና በአሞስ ሳተላይት ጀምሯል።ገዢው ፓርቲ አገሪቱን አንጡራ ሃብት በከፍተኛ መጠን በማፍሰስ ኢሳትን ከአየር ላይ ለማስቀረት የሚያደርገውን ጥረት በቀጠለበት በዚህ ወቅት ኢሳት እንደገና በአሞስ
ሳተላይት ወደ አየር መመለሱን የድርጅቱ ማኔጅመንት አስታውቋል፡፡
ኢሳት ለ24 ሰዓታት በSES 5 አማካኝነት ያለማቋረጥ ለሁለት ዓመታት ሲያቀርበው የቆየው ፕሮግራም ከሰኞ መጋቢት 14/2007 ከአቅም በላይ በሆነ ምክንያት ከተቋረጠ በሁዋላ ፣ በአንድ ወር ጊዜ ውስጥ ተደራሽነቱን በማስፋት
በአዲስ ሳተላይት ስርጭቱን ቢቀጥልም፣ በሳምንታት ጊዜ ውስጥ ገጥሞት ከአየር ላይ ወርዷል።
ምንም እንኳ ድርጅቱ አፈናውን ለማስቀረት የሚቻለውን ሁሉ እያደረገ ቢሆንም ፣ በውጭ አገር ታላላቅ መንግስታት በሚደረግ ግፊት ፣ ለሳተላይት ኩባንያዎች በሚቀርብ የገንዘብ ስጦታና እና ከፍተኛ ጥቅም በሚያስገኙ ፕሮጀክቶች
በመደለል፣ የህወሃት/ኢህአዴግ መንግስት ኢሳት በኢትዮጵያ ምድር እንዳይታይ ከፍተኛ ጥረት እያደረገ ነው።
ማኔጅመንቱ “እነሱ ለአፈና ካላቸው ቁርጠኝነት በላይ እኛም የኢትዮጵያ ሕዝብ የነጻነት ርሃብ ይሰማናል እና ማናችውንም መስዋዕትነት በመክፈል ኢሳት በኢትዮጵያ ውስጥ የኢትዮጵያውያን ድምጽ ሆኖ እንዲቀጥል እንደምንሰራ እያረጋገጥን በአዲስ ሳተላይት እንደገና ስርጭታችን ” መቀጠሉን እናስታውቃለን ብሎአል፡፡
አዲሱ ሳተላይት የሳህን አቅጣጫ በከፊል ማስተካከል የሚጠይቅ ቢሆንም፣ ሕዝቡ የችግሩን ስፋት ግንዛቤ ውስጥ በማስገባት ይህንኑ እንዲፈጽም እንዲሁም በውጭ ሃገር የሚኖሩ ኢትዮጵያውያንና ነጻነት ወዳዶች ሁሉ ኢሳት በተጨማሪ ሳተላይቶች ጭምር ስርጭቱን ለማስፋት የሚያደርገውን ጥረት እንዲደግፉ ማኔጅመንቱ አቅርቧል።
አዲሱ የሳተላይት ስርጭት
Amos,
Frequency 12335 vertical,
symbol rate 27500 (27.5) , FEC 3/4
17 degree east
ሲሆን ኢትዮጵያውያን መረጃውን በማሰራጨት ከኢሳት ጎን እንዲቆሙ ጥሪ አቅርቧል።
ኢሳት በAB 7 ሳተላይት ላይ የ 24 ሰዓታት የራዲዮ ዝግጅት በማቅረብ ላይ መሆኑ ይታወቃል።



No comments:

Post a Comment