Friday, May 1, 2015

የአራት ኪሎ ወጣቶች ለሁለተኛ ጊዜ ታፈሱ


• ‹‹ከአሁን በኋላ በሽብር እንከሳችኋለን!›› ፖሊስ
አራት ኪሎ አካባቢ የሚኖሩ ወጣቶች ትናንት ሚያዝያ 22/2007 ዓ.ም ለሁለተኛ ጊዜ መታፈሳቸውን ወጣቶቹ ለነገረ ኢትዮጵያ ገለጹ፡፡ ከአንድ ወር በፊት ፖሊስ ወጣቶቹን ቪዲዮና ኳስ የሚታይባቸው ቤቶች ውስጥ እያሉ ‹‹ከሰማያዊ ፓርቲ ጋር ግንኙነት አላችሁ›› በሚል ካሰረ በኋላ አስፈርሞና አሻራ ወስዶ እንደለቀቃቸው ገልጸዋል፡፡
በትናንትናው ዕለትም ፖሊስ በርከት ያሉ ወጣቶችን አስሮ የነበር ሲሆን ‹‹ሰማያዊ ፓርቲ እንድትበጠብጡለት ምን ያህል ብር ይከፍላችኋል? ማን ነው ያደራጃችሁ? ደንጋይ ለመወርወር ምን ያህል ብር ይከፈላችኋል?›› በሚል ምርመራ እንደተደረገባቸው ገልጸዋል፡፡ በስተመጨረሻም ምሽት ላይ አስፈርሞና አሻራ ወስዶ ከእስር ተለቀዋል፡፡ ወጣቶቹን ‹‹ከአሁን በኋላ ከሰማያዊ ፓርቲ ጋር ግንኙነት እንዳላችሁ ካወቅን በሽብር ነው የምንከሳችሁ፡፡›› የሚል ማስጠንቀቂያ እንደተሰጣቸው ገልጸዋል፡፡
ነገረ ኢትዮጵያ / Negere Ethiopia


No comments:

Post a Comment