Saturday, May 24, 2014

የኢትዮጵያመንግሥት የጋዜጣናመጽሔት አከፋፋዮችን ያለንግድፈቃድ በመሥራት እናታክስ ባለመክፈል ወንጀል ለመክሰስ እየተዘጋጀ መሆኑ ተሰማ፡፡



ኢሳት ዜና:የጋዜጣና መጽሔት አከፋፋዮች በተለይ መንግሥትን የሚደግፉ ጋዜጣና መጽሔቶችን ሆንብለው ከገበያ ያስወጣሉ በሚል ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የተጠናከረ ትችት ከመንግሥት ባለሰልጣናት በመቅረብ ላይ ሲሆን በአቶ ሬድዋን ሁሴን የሚመራው የመንግስት ኮምኒኬሽንጽ/ቤት እያካሄደ ያለውን ጥናት ማጠናቀቁ ታውቋል።

ምንጮችእንደገለጹትየጋዜጣናመጽሔትአከፋፋዮችንበሕገወጥነጋዴነትከመክሰስጎንለጎንእነሱሲሰሩ የነበሩትን ሥራ በአነስተኛና ጥቃቅን ነጋዴዎች በማስተላለፍ መንግስት በአከፋፋዮች አማካይነት ይደርሳል ያለውን አፈና ለማስቀረት እንደሚቻል ጥናቱ ይጠቁማል፡፡ይህ የመንግሥት ሃሳብ ገናከውጥኑ ተቃውሞ እየቀረበበት የሚገኝ ሲሆን፣ በተለይ የሕትመት ስርጭቱን በተዘዋዋሪ መንገድ መንግስትለመቆጣጠር ማሰቡ መንግስት የፈለገውን ሲያሰራጭ፣ያልፈለገውን እንዲያፍን ዕድል ይሰጠዋል።

በአሁኑ ወቅት በገዢው ፓርቲ ልሳን በሆነው ራዲዮ ፋና ከአከፋፋዮች ጋር በተያያዘ ከጋዜጠኞች ጋር ውይይት እየተካሄደ ሲሆን በተለይ የብሮድካስት ባለስልጣን የቦርድ አባል የሆኑት አቶ ዛዲግ አብርሃ ብዙዎቹ አከፋፋዮች ሕገወጦች መሆናቸውን በመጥቀስ መንግስት እርምጃ ለመውሰድ እያጠና መሆኑን በግልጽ ተናግረዋል፡፡

በዚሁ ፕሮግራም ላይ አከፋፋዮቹ ከውጪገ ንዘብ እየተቀበሉ የተወሰኑ የፕሬስ ውጤቶችን ያፍናሉ የሚሉ ውንጀላዎችም ተደምጠዋል፡፡ ከመጪው ምርጫ ጋር በተያያዘ ገዢው ፓርቲ አይደግፉኝም የሚላቸውን ጋዜጦች በተለያዩ ወንጀሎች እየከሰሰ ከገበያ ሊያወጣቸው እየሞከረ መሆኑን መዘገባችን ይታወቃል።


No comments:

Post a Comment