Friday, May 16, 2014

የኢትዮጵያ አየር ኃይል ካፒቴን አስመራ ላይ ተቃዋሚዎችን ተቀላቀለ፤ * መንግስት አላስተባበለም



ዘ-ሐበሻ እንደዘገበው የኢትዮጵያ አየር ሃይል አባላት ገዢውን የኢሕአዴግን መንግስት በመክዳት ወደ ተለያዩ ሃገራት የሚያደርጉትን ስደትቀጥለዋል። የኤርትራ ሚዲያዎች የመንግስታቸውን ቃል አቀባይ በመጥቀስ እንዳስነበቡት ሰሞኑን የኢትዮጵያ ሚግ 23 አብራሪየሆነው ካፒቴን ዳንኤል የሽዋስ ስርዓቱን ጥሎ አስመራ ገብቷል።


እንደኤርትራ ሚዲያዎች ገለጻ ከሆነ ካፒቴን ዳንኤል የሺዋስ ኤርትራ ከሚገኙ የኢትዮጵያ ተቃዋሚ ኃይሎች ጋር ተቀላቅለዋል።ሚዲያዎቹ በምን መልኩ ወደ አስመራ እንደገባ የገለጹት ነገር ባይኖርም ማዕዶት የተባለው የኤርትራውያን የመረጃ መረብየኤርትራን መንግስት ቃል አቀባይ በመጥቀስ ካፒቴኑ ለኢሳያስ አፈወርቂ መንግስት እጁን የሰጠው ከነ አውሮፕላኑ ነው ሲል ዘግቧል።

የኢሕአዴግ መንግስት በመከላከያ ውስጥ ያለውን የዘር አድልዎና በኢትዮጵያ ህዝብ ላይ እየፈጸመ ያለውን የሰብአዊ መብት ጥሰትበቸልታ መመልከት እያንገፈገፋቸው የሚገኙ የሠራዊቱ አባላት በተለያዩ ጊዜያት እየሸሹ ወደ ኤርትራ በመግባት ተቃዋሚዎችንእንደሚቀላቀሉ በተደጋጋሚ መዘገቡ ይታወሳል።

No comments:

Post a Comment