Monday, May 26, 2014

በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ምተሃታዊ ማጭበርበር ተፈጽሞብናል ያሉ ደንበኞች ቅሬታ አሰሙ


በኢ.ህ.አ.ዴ.ግ መንግስት ከሚተዳደሩ ባንኮች ውስጥ አንዱ እንደሆነ የሚነገርለት የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በአዲስ አበባ ብቻ ከ45 የሚበልጡ ቅርጫፎች እንዳሉት ይታወቃል። ባንኩ ለደነበኞቹ በሚሰጠው የተቀላጠፈ አገልግሎት ከግዜ ወደግዜ አቅሙን እያጎለበት በሃገር ውስጥ ብቻ ከ205 በላይ የሆኑ ቅርንጫፍ መ/ቤቶችን በመክፈት ከ8000 በላይ በሆኑ ሰራተኞች በመታገዝ የአገልግሎት አድማሱን እስከ ጅቡቲ ድረስ ተደራሽ ለማድረግ ቢጠረም በተለያዩ ግዜያት በሚፈራረቁበት አሰታዳሪዎቹ ተቋሙ ቀደም ብሎ የነበረውን ስም እና ዝና ይዞ መቀጠል እንደተሳነው የሚናገሩ ምንጮች ባንኩ ከደንበኞቹ ቆጥሮ የተረከበውን ጥሬ ገንዘብ በእምነት መስጠት እንደተሳነው ይናገራሉ ። በተለይ 1000 እና ከዛ በላይ የሆኑ ተቀማጭ ገንዘቦችን ባንኩ ለደንበኞቹ ሲያስረከብ በባንኩ ማህተም የታሸጉ ባለ መቶ ኖት ብሮች ላይ የሁለት መቶ እና ከዛ በላይ ጉድለት የሚታይባቸው መሆኑን የባንኩ ተገልጋይ
ከቅሬታ አቅራቢዎቹ በመረጃ አስደግፈው ይገልጻሉ።

ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ለተለያዩ ጉዳዩች ከፍተኛ አሃዝ ያለው ገንዘብ በየቀኑ ውጪ የሚያደርጉ ነጋዴዎች ከ2 እስከ 5000 በር እንደሚጎድልባቸው የሚናገሩ ምንጮች ከተጠቀሱት የባንኩ ቅርንጫፍ መ/ቤቶች በቀን በሚሊዮን የሚቆጠር ገንዘብ ከደንበኞች ኪስ እንደሚመዘበር ይናገራሉ ። ባንኩ በስህተት ትርፍ ገንዘብ እንደማይሰጥ የሚናገሩ ቅሬታ አሰሚዎች ጉድለቱ የተለመደ ነው ከማለት ውጭ በባንኩ ፀያፍ ተግባር አቤት ለሚሉት አካል አጥተው በዚህ መንግስታዊ ተቋም ስም በዜጎች ላይ በጠራራ ፀሃይ እይተፈጸመ ባለው ማጭበርበር ማዘናቸውን ይገልጻሉ ። ሰሞኑንን በቅሎ ቤት አካባቢ የሚገኝ ንግድ ባንክ በአደራ ያስቀመጡትን 25 0000 ብር ወጪ ለማድረግ ወደ ቅርጫፍ መ/ቤት ጎራ እንዳሉ የሚናገሩ አንድ እማወራ የባንኩ ሰራተኞች በማህተም አሽገው ለእማኝነት ሁለት የታሸጉ ርብጣ ብሮችን ቆጥረው እንዳስረከቦቸው ጠቅሰው እቤት ደርሰው በተቀሩት ባለመቶ ኖት ብሮች ላይ ቆጠራ ሲያደርጉ 600 በር ጉድለት ማሳየቱን ገልጸው በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ምተሃታዊ ማጭበርበር እንደተፈጸመባቸው የምስክርነት ቃላቸውን ስጥተዋል።


ለደንበኞቻቸው ክበር እና ዴታ የሌላቸው አንዳንድ ስረአት አልበኛ የባንኩ ሰራተኞች ጉዳዩን እንደሚያውቁ የሚናገሩ አንድ በንገድ ስራ ላይ የተሰማሩ የባንኩ ደንበኛ የታሸገው ገንዘብ ይቆጠርልኝ ብለው ጥያቄ የሚያቀርቡላቸውን ተገልጋዩች እንደሚያመናጭቁ ገልጸው ጡንቻው ፈርጠም ያለ እና የመናገር ችሎታ ያለው ተገልጋይ ሲገጥማቸው ሰራተኞች የጎደሉ እሽግ የብር ኖቶች በእጅቸው መዝነው ስለሚለዩቸው ትክክለኛ የሆኑ ርብጣ ብሮች ለናሙናነት ቆጥረው ለተገልጋዩ በማሳየት በተለመደው መተሃታዊ ስልታቸው ለፍቶ ጥሮ ግሮ የሚያመጣውን የኔ ቢጤ የባንኩን ተገልጋይ ያስለቅሳሉ ብለዋል። የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አሽጎ ለተገልጋዩ ያስረከበውን ጥሬ ገንዘብ ከደንበኞች የባንኩ ሰራተኞች ሲረክቡ እንደሚቆጥሩ የሚናገሩ ቅሬታ አሰሚዎች የታሸገው ገንዘብ ለሚያሳየው ጉድለት መፍትሄ ከመሻት ይልቅ ደንበኛው ሃላፊነት እንዲወስድ በማስፈረም በባንኩ ማህተብ ለተፈጸመው ጸያፍ ተግባር ሽፋን ለመስጠጥ ተገልጋዩን ሲያመናጭቁ እና ሲገላምጡ ይስተዋላል ብለዋል ።
ይህ በባንክ ሽፋን በዜጎች ላይ በጠራራ ፀሃይ በሚፈፀመው ዘረፋ የገዢው ፓርቲ ኢ.ህ.አ.ዴ.ግ ባለስልጣናት እጅ ይኑርበት አይኑርበት እስካሁን በተጨባጭ የተረጋገጠ ነገር እንደሌለ የሚናገሩ ምንጮች የኢትዮጵያን ንግድ ባንክ አካባቢ እያገረሸ የመጣውን የተለመደ ግን ለጆሮ የሚቀፍ አሰራር ማየት ተስኖት ስለባንኩ አትራፊነት በየአመቱ የሚደሰኩረው ገዢው የኢ.ህ.አ.ዴ.ግ መንግስት በግንባር ቀደም ሊጠይቀበት እንደሚገባ ያሰምሩበታል ።
ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ መንግስት በሃላፊነት ቦታ ላይ ያስቀመጣቸው አንዳንድ ሃላፊዎች እንዳይንቀሳቀስ ከታገደ ሂሳብ ሚስጥራዊ የይለፍ ቁጥሮችን በስልጣናቸው በመውሰድ በወል የማይታወቅ ገንዘብ በተለያዩ ቤተስቦችቻው ስም ከባንኩ በማውጣት ለግልጥቅማቸው ሲያውሉ በፌዴራል የሥነ ምግባርና የፀረ ሙስና ኮሚሽን እጅ ከፍንጅ ተይዘው ውህኒ ሲወርዱ ማየት የተለመደ በመሆኑ ግዜ ጥብቆ በተገልጋዮች ላይ እያገረሸ የመጣው ይህ መተሃታዊ ማጭበርበር ስረአቱ የፈጠረው ይህ ብልሹ አሰራር አንዱ አካል መሆኑን አያሌ ታዛቢዎች ይናገራሉ፡፡፤በዚህ ዙሪያ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ሃላፊዎች ለማነጋገር ያደረኩት ሙከራ ለግዜው አልተሳካም
Ethiopian Hagere ጅዳ በዋዲ


No comments:

Post a Comment