Thursday, May 24, 2018

በአፋርና አማራ ክልል ድንበር ላይ በተፈጠረው ግጭት የሰዎች ህይወት እያለፈ ነው

(ኢሳት ዜና ግንቦት 16 ቀን 2010 ዓ/ም) በአፋርና በአማራ ክልል አቅራቢያ በደቡብ ወሎ አካባቢ ሰሞኑን የተቀሰቀሰው ግጭት የበርካታ ዜጎችን ህይወት እየቀጠፈ መሆኑን መረጃዎች ያሳያሉ። ሁለቱ ክልሎች ችግሮቻቸውን በውይይት እንደፈቱ በመገናኛ ብዙሃን ተናግረው የነበረ ቢሆንም፣ ግጭቱ እንደገና አገርሽቶ ቁጥራቸው በውል ያልታወቀ ዜጎች ህይወታቸው አልፏል። በግጭቱ ዙሪያ የሁለቱ ክልል ባለስልጣናት እስካሁን የሰጡት መግለጫ የለም።

No comments:

Post a Comment