Thursday, May 31, 2018

ከአለም ሕጻናት ከግማሽ የሚበልጡት በጦርነትና በድህነት እየተሰቃዩ ነው ተባለ

(ኢሳት ዲሲ–ግንቦት 23/2010) ከአለማችን ሕጻናት ከግማሽ የሚበልጡት በጦርነትና በድህነት በመሰቃየት ላይ መሆናቸውን ሴቭ ዘ ችልድረን የተባለው አለም አቀፍ ግብረ ሰናይ ድርጅት ገለጸ።
መቀመጫውን በዩናይትድ ኪንግደም ያደረገው ሴቭ ዘ ችልድረን ትላንት ይፋ ባደረገው ሪፖርት በትንሹ 1 ነጥብ 2 ቢሊየን የአለማችን ሕጻናት ለከፋ ችግር ተጋልጠዋል። 1 ቢሊየን ያህል ሕጻናት የሚኖሩት ድህነት በተስፋፋባቸው ሀገራት ነው።
240 ሚሊየን ሕጻናት ደግሞ ግጭት በቀጠለባቸው ሀገራት የሚኖሩ መሆናቸውን ሴቭ ዘችልድረን አስታውቋል።
እንደ አለም አቀፉ ግብረሰናይ ድርጅት ሪፖርት ከሆነ 575 ሚሊየን ሕጻናት የጾታ አድሎ በሚካሄድባቸው ሃገራት ውስጥ ይኖራሉ።

No comments:

Post a Comment