Thursday, May 31, 2018

የጋምቤላ ክልል ፕሬዚዳንት ዶ/ር ጋትሎክ ቱት ውጭ አገር ሄደው እንዲታከሙ የክልሉ ካቢኔ ከክልሉ መጠባበቂያ በጀት 1 ሚሊዮን ብር ወጪ እንዲሆን ወሰነ።

(ኢሳት ዜና ግንቦት 23 ቀን 2010 ዓ/ም) የክልሉ ምክር ቤት ለክልሉ ፋይናንስ ክፍል በላከው ደብዳቤ ላይ ርዕሰ መስተዳድሩ ዶ/ር ጋትሎክ ቱት ህክምናቸውን በጦር ሃይሎች ሆስፒታል ሲከታተሉ ቢቆዩም፣ ለውጥ ሊታይ ስላልቻለ ወደ ውጭ አገር ሄደው የተሻለ ህክምና እንዲያገኙ 1 ሚሊዮን ብር እንዲሰጣቸው የክልሉ መንግስት ካቢኔ በሙሉ ድምጽ መደገፉን ገልጿል። ገንዘቡ ከመጠባበቂያ በጀት በክልሉ የግዢ የስራ ሂደት አስተባባሪ በሆኑት አቶ ማቲዎስ ገለታ ስም ወጮ ተደርጎ ለርዕሰ መስተዳደሩ እንዲከፈልም ደብዳቤው ያዛል።

No comments:

Post a Comment