Tuesday, May 8, 2018

የታገዱት የአየር ሃይል አብራሪዎች መፍትሄ እንዲሰጣቸው ጠየቁ

 (ኢሳት ዜና ሚያዝያ 30 ቀን 2010 ዓ/ም) በተለያዩ የአገሪቱ ክፍሎች የተካሄዱትን ተቃውሞዎች ተከትሎ ከ2 አመት ላላነሱ ጊዜ ከስራ የታገዱ የአማራ እና የኦሮሞ ብሄር ተወላጅ የሆኑ የአየር ሃይል አብራሪዎች ለምን እንደታገዱ ማብራሪያ እንዲሰጣቸው ጠየቁ። በምስራቅ አየር ምድብና በማእከላዊ አየር ምድብ ያገለገሉ የነበሩት አብራሪዎች “ ጥፋታችን ምንድነው? ስራ እንድናቆም የታዘዝነውስ ለምንድነው?” የሚል ጥያቄ አቅርበዋል። የስርዓቱ ደጋፊዎች የሆኑት የትግራይ ተወላጆች ሰላም ለማስከበር በሚል ወደተለያዩ አካባቢዎች በመጓዝ ከፍተኛ ጥቅማጥቅም እንዲያገኙ እየተደረገ ሲሆን፣ ሌሎች ግን በብሄራቸው ብቻ ጥቅማጥቆምችን እንዲያገኙ እንደማይደረግ ምንጮች ገልጸዋል። ባለፉት ሁለት አመታት በርካታ የአየር ሃይል አብራሪዎች ከስራቸው ታገደዋል። ሌሎች ደግሞ ስርዓቱን አናገለግልም በማለት ከአገር ወጥተዋል።

No comments:

Post a Comment