Tuesday, May 29, 2018

በኢትዮጵያ ስርነቀል ለውጥ እስከሚመጣ ትግላቸውን አጠናክረው እንደሚቀጥሉ ብረት ያነሱ አርበኞች ገለጹ።

በሰሜን የኢትዮጵያ ክፍል በተለያዩ አካባቢዎች የትጥቅ ትግል በማድረግ በአገዛዙ የተለያዩ ወታደራዊና መንግስታዊ ተቋማት ላይ ጥቃት በመሰንዘር ላይ የሚገኙት አርበኞች ሰሞኑን በአማራ ክልል መገናኛ ብዙሃን እየቀረበ ያለው ዜና ከእውነት የራቀ ነው ሲሉ አስተባብለዋል። ሁለት የአርበኛ መሪዎች ወደ አገዛዙ የገቡበት ምክንያት ከጤና ጋር የተያያዘ ነው ያሉት አርበኞች ትግሉን ከድተው እንደገቡ ተደርጎ የሚቀርበው ፕሮፖጋንዳ ህዝቡን ለማደናገር ሆን ተብሎ የተዘጋጀ ነው ሲሉ ከኢሳት ጋር ባደረጉት ቆይታ ገልጸዋል። አሁንም በረሃ ላይ ነን፡ በኢትዮጵያ እውነተኛ ለውጥ እስከሚመጣ ትግሉ ይቀጥላል ብለዋል።

No comments:

Post a Comment