
ሌላ አምባገነን አገዛዝ መሸጋገር አይደለም። እናም ሕዝቡ ያለ የሌለ ሃይሉን ተጠቅሞ ይህን የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ይሰብረዋል ነው ያሉት። ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በቪዲዮ በተለቀቀ መልዕክታቸው እንዳሉት የሕወሃት ኢሕአዴግ አገዛዝ እየተፍረከረከና እያከተመለት መሆኑን የሚያሳዩ በርካታ ምልክቶች መታየት ጀምረዋል። የጠቅላይ ሚኒስትር ሃይለማርያም ደሳለኝ የስልጣን መልቀቂያ ጥያቄ፣ በኢሕአዴግ ውስጥ ባሉ አባል ድርጅቶች የለውጥ ፍላጎት ያላቸው ሃይሎች መፈጠር መጀመራቸው፣ የትግሉ ውጤት ስኬታማ መሆኑን እንደሚያመለክትም ገልጸዋል። በዚህ የለውጥ ሂደት ወገኖቻችን የታሰሩበት፣የተገረፉበትና የተገደሉበት ትግል ሃላፊነት በሌላቸው ሃይሎች እጅ እንዳይገባም ጥንቃቄ መደረግ ይኖርበታል ብለዋል። እናም የምንታገልለት ለውጥ የኢትዮጵያን ሕዝብ ይሁንታ ባገኘበት ሁኔታ የሽግግር መንግስት የሚፈጥር መሆን አለበትም ነው ያሉት።ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ። ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ዋናው የትግል ስልታችን ሕዝባዊ እምቢተኝነት ነው ሲሉም ገልጸዋል። በዚሁ ትግል ታዲያ በኑሮ ውድነት እየተንገላታ ያለው የአዲስ አበባ ሕዝብም ዝምታውን ሰብሮ ትግሉን እንዲቀላቀል ጠይቀዋል። ለመከላከያ፣ለኢሕአዴግ አባላትና ለትግራይ ሕዝብም አገዛዙ እያከተመለት በመሆኑ ከአገዛዙ መደበቂያነት ወጥተው የሕዝቡን ትግል እንዲቀላቀሉ ጥሪ አቅርበዋል።
No comments:
Post a Comment