Thursday, July 31, 2014

ሸራተን ሆቴል ብዛት ያላቸውን ሰራተኞቹን አባረረ

በሼህ አላሙዲን ሜድሮክ ኩባንያ ስር የሚገኘው ሸራተን አዲስ ሆቴል አስተዳደር ከሰራተኛ ማህበሩ ጋር ለአመታት የዘለቀ ግጭት ውስጥ መክረሙን የሚያስታውሱት ምንጮች በዛሬው ዕለት አስተዳደሩ የማህበሩን አመራሮች ጨምሮ በስራ ገበታቸው ተገኝተው የነበሩ ብዛት ያላቸውን ሰራተኞች ‹‹ሆቴሉ ከእናንተ ጋር የነበረውን የስራ ኮንትራት አቋርጧል››የሚል ወረቀት በመስጠት ከ15 ዓመታት ያላነሰ ድርጅቱን ያገለገሉ ሰራተኞቹን ማባረሩ ታውቋል፡፡
የስራ ዩኒፎርም ለብሰው ወደ ስራቸው ለመግባት ይዘጋጁ የነበሩት ሰራተኞች ወደ ቢሮ ተጠርተው ወረቀቱን መቀበላቸውን እንዲፈርሙ እየተደረጉና በሆቴሉ የጥበቃ ሰራተኞች ታጅበው ግቢውን እንዲለቁ መደረጋቸውን ምንጮች አስረድተዋል፡፡
መረጃውን ተከትሎ ወደ ሆቴሉ አስተዳደር ስልክ ብደውልም ሃላፊ የተሰኙት ሰው ስማቸውንና በሆቴሉ ውስጥ ያላቸውን የስራ ድርሻ ጨምሮ ድንገተኛው የሰራተኛ ስንብት ስለመፈጸሙ ወይም ስላለመፈጸሙ ለመናገር ፈቃደኛ ሳይሆኑልኝ ቀርተዋል፡፡


No comments:

Post a Comment