Sunday, July 20, 2014

ምናምንቴዎች በሠለጠኑ ግዜ ህዝብ ያልቀሳል !!!

ኢትዮጵያ ላይ ጥቂት ምናምንቴዎች ሰልጥነው ህዝቡን እያስለቀሱት ነው። ኢትዮጵያዊያን ለብዙ ዘመን በብዙ ሃዘንና እንባ ውስጥ መኖራቸው የታወቀ ነው። የአሁኑ ሃዘን እንዲሁ ተራ ሃዘን፤ ልቅሶውም ተራ ልቅሶ አይደለም። መራር ሮሮ እንጂ። ይህን የህዝብ ሮሮ የሚሰማ መንግስታዊ አካልም የለም። በ“Global terrorist database” ውስጥ የሥም ዝርዝሩ ተመዝግቦ የሚገኘው “የትግራይ ህዝብ ነፃ አውጪ” ነኝ የሚለው ቡድን መንግስ ነኝ ቢልም የመንግስት መልክና ባህሪይ ሊኖረው አልቻለም። ህወሃት መንግስታዊ አሸባሪ እንጂ የኢትዮጵያ መንግስት ለመሆን የሞራልም ሆነ የእውቀት ብቃት ያለው ቡድን አይደለም።


ህወሃት ከተፈጠረ ጀምሮ የብዙ ንፁህ ዜጎችን ደም አፍሷል። ብዙ ዜጎችን ለስቃይ እና ለስደት ዳርጓል። ብዙ ቤተሰብን በትኗል። በተለይ ጠላቴ ነው ብሎ የሚያምነውን የአማራ ህዝብ ለማጥፋት ሴቶችን መካን የሚያደርግ ክትባት እስከ መከተብ ደርሷል። በዚህም የአማራው ቁጥር ከነበረው ቀንሶ ተገኝቷል። ይህ አሸባሪ ቡድን በኦጋዴን፤ በአፋርና በጋምቤላ የፈፀመውን የዘር ማጥፋት ወንጀል ዓለም ያወቀው ነው። በኦሮሚያ የፈሰሰው የንፁሃን ዜጎች ደም ከምድር ወደ ሰማይ እየጮኸ ነው። በአዲስ አበባ እና በደቡብ የተበተነውን የቤተሰብ ብዛት ቆጥረን አንዘልቀውም። በትግራይ የሚገኙ ምርጥ ኢትዮጵያውያን በሙሉ አልቀዋል። የተረፉ ጥቂቶች ቢገኙም መግቢያ መውጪያ አጥተው በሁለት ሰይፍ የሚቆረጡ ሁነዋል።

የትግራይ ነፃ አውጪዎች ያተረፉልን ነገር ቢኖር ውርደት ነው። ውረድቱ የከበዳቸው ዜጎች ራሳቸውን በእሳት አቃጥለዋል። ገደል ውስጥ ራሳቸውን ወርውረው የሞቱም አሉ። ህወሃቶች ባሉበት ከምንኖር ብለው ስደተን መርጠው የበርሃ ንዳድ፤ የባህር ዐዞ እራት የሆኑ ብዙ ናቸው። በባእዳን አገር ውስጥም ማረፊያ አጥተው የሚንከራተቱም ቁጥራችው በቀላል የሚገመት አይደለም። ይህ የህወሃት መራር ፍሬ ነው።

አዎን በአገራችን ላይ እነዚህ እግዜርን የማያውቁ የሰይጣን ድንኳኖች ከሰለጠኑ ዘመን ጀምሮ የንፁህ ሰው ደም ሳይፈስ የዋለበት ቀን የለም። ህወሃቶች የትልቁንም የትንሹንም ደም በማፈሰስ የሚረኩ፤ ቤተሰብንም በትነው ድሃ አደግ በማድረጋቸው የሚደሰቱ ፍጡራን ስለመሆናቸው የእስከዛሬው ምግባራቸው ቋሚ ምስክር ነው። ለስልጣን ካላቸው ሥሥት የተነሳም ከባዕዳን ጋር እየተመሳጠሩና ብዙ ሚሊዮን ገንዘብ እየከፈሉ ነፍሰ ገዳዮችንና አፋኞችን ቀጥረው ዜጎችን እስከማሳፈን ደርሰዋል። የዚህ ዕኩይ ተግባር ሰለባዎች ብዙ ናቸው። ታላቁ ሰው አንዳርጋቸው ፅጌ የዚህ እኩይ ተግባር ሰለባ ከሆኑ ብዙ ኢትዮጵያዊያን መካከል አንዱ ነው።

ጠላቶቻችን(ህወሃቶች) እና ወዳጆቻችን በሙሉ ስሙን ! አንዳርጋቸው የተነሳው ፡

ሚዛኑን ስቶ መሳለቂያ የሆነው ፍትህ ወደ ሚዛኑ ለመመለስና ፍጹም የህግ የበላይነትን በአገራችን ለማስፈን ነው።

ግንቦት ሰባትንና መሪውን አንዳርጋቸው ፅጌን በህወሃቶች ዘንድ አሸባሪ እንዲሆኑ ያደረጓቸው እነዚህ ከላይ ለመዘርዘር የሞከርናቸው ቁም ነገሮች ናቸው እንጂ እንደ ህወሃቶች ግንቦት ሰባት ባንክ ሲዘርፍ፤ የእምነት ሥፍራዎችን ሲያወድም፤ ትምህርት ቤቶችን ሲያፈራርስ፤ የቀደመው ትውልድ በደምና አጥንቱ ያቆየውን ድንበር ቆርሶ ሲሸጥ፤ የአገሪቷን ለም መሬት ለባእዳን ሲሸጥ፤ አንዱን ጎሳ ከሌላው ጋር አጋጭቶ ደም እንዲፈስ ሲያደርግ ተገኝቶ አይደለም።

ባንክ መዝረፍ፤ የእምነት አምባዎችን ማርከስ፤ ትምህርት ቤቶችን ማውደም፤ የአገሪቷን ድንበር እያፈርሱ ለባዕዳን አሳልፎ መስጠት፤ ለም መሬቶችን ለባዕዳን መቸብቸብ፤ በህዝቦች መካከል ጥላቻን መዝራት፤ ከድሃ ጉሮሮ ላይ ሠርቆ በውጪ አገራት ባንኮች ውስጥ ገንዘብ ማጠራቀም ህወቶች እንደ ሙያ የተያያዙት የእለት ተዕለት ተግባራቸው ነው። ግንቦት ሰባት የተነሳው እንዲህ ዓይነት ነውረኞችን ከተቆናጠጡበት የስልጣን ወንበር ላይ አውርዶ ኢትዮጵያ ለኢትዮጵያዊያን የምትሆን አገር እንድትሆን ለማድረግ ነው። የመሪያችን የአንዳርጋቸው ፅጌም ምኞት ይሄው ነው። ኢትዮጵያን ከጥቂት ዘረኞችና ዘራፊዎች እጅ አውጥቶ የብዙሃኑ ኢትዮጵያዊ አገር እንድትሆን ማድረግ።

ይሄ የኢትዮጵያ ውድ ልጅ በነውረኞቹ የትግራይ ነፃ አውጪዎች እጅ ገብቷል። ነፃ አውጪ ነን ባዮቹ አንበሳውን ከበው ለመቦጫጨቅ እንደሚያጓሩ ጅቦች ዓይናቸውን አጉረጥርጠው እያሰቃዩት ይገኛሉ። ምንም እንኳ ይሄ ታላቅ ሰው በነፍሰ ገዳዮቹ እጅ ቢወድቅም እርሱ የጀመረው የነፃነት ጥያቄ የሚሊየኖች ጥያቄ ሆኖ ከመቸው ግዜ በላይ ሚሊየኖችን አስነስቷል። በዓለም ዙሪያ “እኔም አንዳርጋቸው ነኝ፤ እኔም ግንቦት ሰባት ነኝ” የሚሉ ድምፆች ከፍ ብለው እየተሰሙ ነው። አንዳርጋቸውን ማሰር እንጂ እርሱ የጀመረወን የነፃነት ጥያቄ፤ እርሱ የዘረጋውን የትግል መስመር ማሰር አይቻልም። ለዚህም ነው አንዳርጋቸው የማይጨበጥ ፅኑ መንፈስ ነው የሚባለው።

ግንቦት ሰባት የፍትህ፤ የነፃነትና የዴሞክራሲ ንቅናቄ ህወሃት የተባለው ዘረኛ እና የወሮበላዎች ቡድን የገነባው የሰይጣን ድንኳን ፈርሶ ፍትህ፤ነፃነት እና እውነተኛ ዴሞክራሲ ተገንብቶ እስከሚያይ ድረስ የጀመረውን ሁለ ገብ ትግል አጠናክሮ ይቀጥላል።

የተከበራችሁ ያገራችን ዜጎች ሆይ ስሙን ! እኔም አንዳርጋቸው ነኝ ማለታችሁ አንድ በጎ እርምጃ ነው። እኔም አንዳርጋቸው ነኝ ማለት አንዳርጋቸው ራሱን አሳልፎ ለሰጠው ድንቅ ዓላማ ራሳን አሳልፎ መስጠት ማለት መሆኑንም መረዳት ያስፈልጋል። አንዳርጋቸው የቆመለትን ዓላማ ለማስፈፀም እኛ ወደ እናንተ እሰከምንመጣ መጠበቅ የለባችሁም። በያላችሁበት አምስትም ስድስትም አስርም እየሆናችሁ የአርበኝነት ተግባር መፈፀም መጀመር አለባችሁ። የቀደመዉ ትውልድ ፋሽት ጣሊያንን በየመንደሩ እየተደራጀ እና የጎበዝ አለቃ እየመረጠ መፋለሙን አስታወሱ። እናንተም ከምታምኑት ጋር እየተደራጃችሁና የጎበዝ አለቃ እየመረጣችሁ የዘመኑን ፋሽስት ልትፋለሙት ይገባል። ዘመቻ አንዳርጋቸው ማለት እኔ ለነፃነቴ፤ እኔ ለፍትህ እና ለህግ የበላይነት፤ እኔ ከዘረኞቹና ከሌቦቹ ህወሃቶች የፀዳች አገር ለመፍጠር ተነስቼአለሁ ማለት ነው። ለዚህም ዓላማ ለመሞትና ለመግደል ዝግጁ ነኝ ልትሉ ግዜው አሁን ነው። እንደ ቀድሞ ዝም ብላችሁ የምትሞቱ ሳትሆኑ ለመግደልም የምትችሉ መሆኑን በተግባር ማሳየት መቻል አለባችሁ።

“ትግሬን ነፃ” እናወጣለን ብላችሁ የተነሳችሁ እናንት ነውረኞች ሆይ ስሙ ዓይናችሁ እያየ፤ ጆሯችሁም እየሰማ ከወገኖቻችን ጎን ሁነንና እጅ ለእጅ ተያይዘን ልትገነቡ የሞከራችሁትን የዘረኝነትና የዝሪፍያ መረብ እንበጣጥሰዋለን። እናንተ ዘረኞችና ዘራፊዎች ስሙ! ህዝብን እንዳስለቀስዋችሁ መቀጠል እንደማትችሉ እርግጠኛ ሁኑ። አገራችን ኢትዮጵያም እናንተን ከመሰሉ ምናምንቴዎች ፀድታ ህዝቦቿም በነፃነት የሚኖሩበት ግዜ እሩቅ አይደለም። ያን ግዜ በእናንተ ነውሮኞች ግፍ የሚያለቅስ ህዝብ አይኖርም። አበቃን!!!

ድል ለኢትዮጵያችን ይሁን !!!!


No comments:

Post a Comment