Wednesday, July 16, 2014

በሃረማያ ዩኒቨርሲቲ ዓመፅ ተጀመረ…!!!

የሃረማያ ዩኒቨርሲት የድህረ ምረቃ ተማሪዎች የመመረቅያ ፅሑፍ ክፍያ ከዕጥፍ በላይ በመጨመሩ ዓመፅ ኣስነስተዋል።

ተማሪዎቹ ከትናንት በስትያ ሰኞ ሓምሌ 7 /2006 ዓ/ ም ክፍያው 3000ብር እንደሆነ ከዩኒቨርስቲው ሬጅስትራር የተፃፈ ደብዳቤ የተሰጣቸው ቢሆንም ዩኒቨርሲቲው ሃሳቡ በመቀየር ክፍያው ወደ 8700 ብር ከፍ በማድረግ በቦርድ ለጥፎዋል።

ተማሪዎቹ ተሰባስበው ወደ ዩኒቨርሲቲው ሃላፊዎች የሄዱ ሲሆኑ ክፍያው ከዕጥፍ በላይ እንዲሆን የተደረገበት ወሳኔ ኣግባብነት እንደሌለውና ወደ ቀድመው መጠን ካልተስተካከለ እንደማይመዘገቡ ኣሳውቀዋል።

እንደምጫችን ኣገላለፅ ከሆነ ክፍያው ባንዴ ከእጥፍ በላይ እንዲሆን የትደረገው የመንግስት ሰራተኞች ደምወዝ ጭማሪ ተደርገዋል የሚል እንደሆነ ኣረጋግጠዋ።

የዩኒቨርስቲ ኣስተዳደር በጉዳዩ ኣስቸኳይ ስብሰባ እያካሄደ እንደሆነም ለማወቅ ተችለዋል።

ሃረማያ ዩኒቨርስቲ ልማታዊ መንግስታችን ስግብግብ ዩኒቨርሲት ብሎ ታፔላ እንደሚለጥፍለት ይጠበቃል።

“ስግብግብ ነጋደዎች” ነው…! ያለው በኢቲቪ እየተናገረ የሰማሁት ኣንዱ ቱባ ባለስልጣን።

ዓመፁ በኣግባቡ ይፈታ ይሆን? ወይስ እንደተለመደው መቺ ሃይል ይላካል…?


No comments:

Post a Comment