Monday, April 2, 2018

በእስር ላይ የሚገኙት ፖለቲከኞችና ጋዜጠኞች አሁንም በችግር ላይ ናቸው

 (ኢሳት ዜና ማጋቢት 24 ቀን 2010 ዓ/ም) ከሳምንት በፊት ያልተፈቀደ ስብሰባ እና አርማ የሌለውን የኢትዮጵያን ሰንደቃላማ ተጠቅማችሁዋል በሚል በእስር ላይ የሚገኙት እነ ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ አሁንም ያሉበት ሁኔታ አለመሻሻሉ ታውቋል። አቶ አንዱአለም አራጌ፣ ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ፣ ተመስገን ደሳለኝና ሌሎችም ፖለቲከኞችና ጋዜጠኞች የታሰሩበት ሁኔታ እጅግ መጥፎ የሚባል መሆኑ መዘገቡ ይታወቃል። በአገራቸው ጉዳይ ምንም አይነት መረጃ እንዳያገኙ ተደርገው መታሰራቸውንም ምንጮች ገልጸዋል።

No comments:

Post a Comment