Monday, August 27, 2018

የቀድሞ የብአዴን ከፍተኛ አመራርና የኢህአዴግ ቁልፍ ሰው አቶ በረከት ስምዖን የመንቀሳቀስ መብቴ ተገድቧል ሲሉ ገለጹ።

(ኢሳት ዲሲ–ነሐሴ 21/2010)
ታዲያስ አዲስ ከተሰኘ የሬዲዮ ፕሮግራም ጋር ባደረጉት ቃለመጠይቅ አሁን ባለው ሁኔታ በሀገሪቱ የተለያዩ ቦታዎች ለመንቀሳቀስ ገደብ ተጥሎብኛል ብለዋል።

አቶ በረከት የመንቀሳቀስ መብታቸውን የገደበው የመንግስት አካል ይሁን ሌላ በግልጽ ያስቀመጡት ነገር የለም። የብአዴን የአሁኑን አመራር ክፉኛ የወቀሱት አቶ በረከት ስምዖን የተበላሹ አመራሮች ናቸው ሲሉም ኮንነዋቸዋል።

አሁን በመሪነት የተቀመጡት የብአዴን ሰዎች ወደ አደገኛ አቅጣጫ እያመሩ በመሆኑ ህዝቡ ሊያስቆማቸው ይገባል በማለት ገልጸዋል።

No comments:

Post a Comment