Thursday, August 30, 2018

የመከላከያ ስራዊት ንብረት የሆነ አውሮፕላን ተከስክሶ 18 የሰራዊት አባላት እና ሲቪሎች ህይወታቸው አለፈ

 ( ኢሳት ዜና ነሐሴ 24 ቀን 2010 ዓ/ም ) የመከላከያ ሰራዊት የኢንዶክትሪኔሽን ዋና ዳይሬክቶሬት ባወጣው መግለጫ የበረራ ቁጥሩ 808 የሆነ የአየር ሃይል አውሮፕላን ለስራ ጉዳይ ከድሬዳዋ ወደ ደብረዘይት እየተጓዘ ለማረፍ 20 ደቂቃዎች ሲቀሩት ኤጂሬ በተባለው ቦታ ላይ ወድቆ የሰዎች ህይወት አልፏል። የአደጋው መንስዔም በባለሙያዎች እየተጣራ መሆኑን አስታውቋል። በአደጋው 15 የመከላከያ ሰራዊት አባላት እና 3 ሲቪሎች ህይወታቸው አልፏል።

No comments:

Post a Comment