Monday, August 27, 2018

የኢትዮጵጣ አየር ትራፊክ ተቆጣጣሪዎች የስራ ማቆም አድማ በማድረግ ላይ ናቸው

 ( ኢሳት ዜና ነሐሴ 21 ቀን 2010 ዓ/ም ) በቦሌ ፣ በባህርዳርና መቀሌ የሚገኙ የአየር ትራፊክ ተቆጣጣሪዎች አድማ ቢመቱም ፣ የበረራ አገልገሎት ግን አልተቋረጠም። የስራ ማቆም አድማ መነሻው ከደሞዝና ከተለያዩ ጥቅማጥቆሞች ጋር የተያያዘ ሲሆን፣ ማኔጅመንቱ ለጥያቄያቸው በቂ ምላሽ አልሰጠም። የሲቪል አቭዬሽን ባለስልጣን አድማ በመቱ ሰራተኞች ቦታ በጡረታ የተገለሉና በተለያዩ ምክንያቶች አገልግሎት ያቋረጡ ሰዎችን በማሰማራት ችግሩን ለመቅረፍ እየሞከረ ነው።

No comments:

Post a Comment