Wednesday, June 17, 2015

ምክትል ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ብርሃነ ገብረ ክርስቶስ ትላንት ምሸት በድብቅ ጅዳ ገቡ

ሰኔ 8 ቀን 2007 ምሸት ሳውዲ አረቢያ የገቡት የኢትዮጵያው ምክትል ውጭ ጉዳይ ሚንስተር ጉብኘት ያለተጠበቀና እንግዳ መሆኑን የሚናገሩ የጅዳ ቆንስላ ጽ/ቤት ምንጮች በዲፕሎማቱ ዘንድ ከፍተኛ መደናገጥ መፈጠሩን ገልጸዋል፡፤ ሚንስትሩ ከሳውዲ ከፍተኛ ባለስልጣናት ጋር ለመገናኘት ውጭ ጉዳይ ሚንስቴር መ/ቤት ቢሄዱም የኢ.ህ.አ.ዴ.ጉ ከፍተኛ ባለስልጣን ጉብኝት ኦፊሴላዊ ይሁን በድብቅ እስካሁን የሚታወቅ ነገር እንደሌለ ጅዳና ሪያድ ያሉት የመንግስት ዲፕሎማቶች ምንም አይነት ነገር እንደማያውቁ ከቆንስላው ጽ/ቤትና ከሪያድ የኢትዮጵያ ኤንባሲ የሚወጡ መረጃዎች ያመለክታሉ።
የሚንስትሩን ድንገተኛ ጉብኝት ተከትሎ ማምሻውን ከውጭ ጉዳይ ሚንስትሩ ጋር ለመወያየት ሽርጉድ ይሉ የነበሩ የጅዳና አካባቢው ካድሬዎች ፡ የልማት ማህበራት ተወካዮች ለደጋፊዎቻቸው በሚስጠር ጥሪ ማስተላለፋቸውን የሚቃወሙ ኢትዮጵያውያን ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣኑ በዚህ መልክ ወደ ጃዳ መግባታቸው ዲፕሎማት ብለው ለሾሞቸው አገልጋዮቻቸው ያላቸውን ንቀት የሚያሳይ ብቻ ሳይሆን በዲፕሎማቱ ላይ እምነት እንደሌላቸው አመላካች መሆኑን ይናገራሉ። ከቀርብ ግዜ ወዲህ የኢ.ህ.አ.ዴ.ግ ከፍተኛ ባለ ስልጣናት ለስራ ጉብኘትም ይሁን ለህክምና ወደ ሳወዲ አረቢያ ሲገቡ የኤንባሲው ዲፕሎማቶች መረጃ የሚያገኙት ከተለያዩ ድህረ ገጾች መሆኑን የሚናገሩ ውስጥ አዋቂዎች ከአንድ አመት በፊት አቶ በረከት ስመኦን በሚስጠር ለህክምና ሲገቡ ዲፕሎማቱ በተመሳሳይ ሁኔታ መረጃ እንዳልነበራቸው ያስታውሳሉ ፡፤
በሳውዲያዊው ቱጃር ሼክ አላሙዲን የግል አውሮፕላን ተጭንው እኩለ ለሊት ሳውዲ የገቡት አቶ በረከት ስመኦን ጅዳ ከተማ የሚገኝ አንድ ሆስፒታል ውስጥ በህክምና ላይ መሆናቸውን የቆንሳላ ጽ/ቤቱም ይሁን በሪያድ የኢትዮጵያ ኤንባሲ ያወቁት ጎልጉል እና ዘሃበሻ ሚዲያ ላይ በተለቀቀው መረጃ መሆኑን የሚገልጹ እነዚህ ወገኖች በዲፕሎማቱና በመንግስት መሃከል ከፍተኛ የሆነ የመረጃ ክፍተት መኖሩን በማውሳት የመረጃ ክፍተቱን ለማሞላት ዲፕሎማቱ ሚስጥራዊ መረጃዎችን ለማግኘት የተጠቀሱትን ሚዲያዎች መከታተል አማራጭ የሌለው መፍትሄ እንደሆነባቸው ይነገራል። ዛሬ በጅዳ ቆንስላ ጽ/ቤት በተደረገው ስብሰባ ላይ የታዩት ሚንስቲር ገብረክርስቶስ በሙስና ስለ ሚታመሰው በጅዳ የኢትዮጵያ ኮሚኒቲ ት/ቤትና ህልውናው ስላከተመው በሪያድ የኢትዮጵያ ኮሚኒቲ ማህበር ንብረት መባከን ምንም መረጃ እንደሌላቸው ለማወቅ ተችሏል ። አንድ የውጭ ጉዳይ ሚንስቴር መ/ቤት ሰራተኛ አስከትለው ትላንት ጅዳ ሳውዲ አረቢያ ስለገቡት ምክትል ውጭ ጉዳይ ሚንስቲር ብርሃነ ገብረ ክርስቶስ ጉብኘት በሳውዲም ይሁን በኢትዮጵያ መንግስት መገናኛ ብዙሃን እስካሁን ምንም የተባለ ነገር እንደሌለ ለማወቅ ተችሎሏ፡፤ዘግይቶ የድረሰን ዜና የመንግስት ከፍተኛ ባለስልጣኑ ወደ ሪያድ ከተማ እንደሚያቀኑ የቆንስላው መረጃዎች ገልጸዋል


No comments:

Post a Comment