Sunday, November 23, 2014

ሰበር ዜና የበይነ መረብ ዘመቻው ኢህአዴግን አሳስቦታል

አንድነት ፓርቲ በሚቀጥለው ሳምንት እንደሚያካሂድ ይፋ ያደረገው የበይነ መረብ ዘመቻ ግቡን እንዳይመታ በቅርቡ አሰልጥኖ ባሰማራቸው የፌስ ቡክ ተጠቃሚዎች ብሄርን፤እምነትን እና የአንዱ ፓርቲ ደጋፊና የሌላው ፓርቲ ነቃፊ በመሆን አጀንዳዎን በማንሳት የፌስ ቡክ ተጠቃሚዎችን ትኩረት ለመሳብና የፌስ ቡክ ተጠቃሚዎች ወደ ጋራ አጀንዳ እንዳይሰባሰቡ ሳምንቱን ሙሉ በንቃትና በጥንቃቄ መስራት እንዳለባቸው በኢህአዴግ ጽ/ቤት በኩል በዛሬው እለት ማስጠንቀቂያዊ ትዕዛዝ መተላለፉን ማስጠንቀቂያው የደረሳቸው ተሳታፊ ውስጥ አዋቂ ምንጮቻችን ገልፀዋል ፡፡እንደ ውስጥ አዋቂ ምንጮቻችን ገለፃ ምን አልባትም ዘመቻው ትኩረት እየሳበ የሚሄድ ከሆነ በቴሌ አማካኝነት የኔት ወርክ መስተጓጎል እና ማቋረጥ ለመፍጠርም መታሰቡን አያይዘው ገልፀዋል፡፡አንድነት ፓርቲ የበይነ መረብ ዘመቻ በቀጣይ ሳምንት እንደሚያደርግ በትላንትናው እለት ለመገናኛ ብዙሀን ይፋ ማድረጉ ይታወሳል፡፡


No comments:

Post a Comment