Tuesday, November 25, 2014

በለገጣፎ ከተማ ከ32,000 ሺህ በላይ ዜጐች ቤት አልባ ሊሆኑ ነው

ነዋሪዎቹ እንደሚሉት ለ12 ዓመታት በአካባቢው መኖሪያ ቀልሰው ኖረዋል፡፡ ሆኖም “የከተማ ሰው ወሮናል” የሚል ተቃውሞ በገበሬው እንዲነሳ ያደረጉ የከተማው ባለሥልጣኖች በ2 ቀናት ውስጥ ቤታችን ሊያፈርሱ ተዘጋጅተዋል ብለዋል፡፡ የካ ሰዴን ወረዳ የሚገኙት የጉራ፣ሰፈራ፣ድሬ፣ ዳሌ እና ቀርሳ የሚባሉ አካባቢዎች ውስጥ የሚገኙ ወደ 3000 ሺህ የሚጠጉ ቤቶች እንዲፈርሱ ምልክት ተደርጎባቸዋል፡፡

ነዋሪዎቹ ቅዳሜ ህዳር 13 ቀን 2007ዓ.ም በከተማው በመሰባሰብ ተቃውሞአቸውን አሰምተዋል፡፡ በነጋታው እሁድ ዕለትም ከ1000 በላይ የሚሆኑ ነዋሪዎች በመሰባሰብ ባጋጠማቸው አደጋ ዙሪያ ተወያይተዋል፡፡ የነዋሪዎቹን ችግር ለማዳመጥ ፈቃደኛ ያልሆኑት የከተማው የመንግስት ባለስልጣናት ግን በቅዳሜው በስብሰባው ላይ ባለመገኘታቸው ነዋሪዎቹ በነጋታው እሁድ ከ1000 በላይ የአካባቢው ነዋሪዎች በወረዳው ጽ/ቤት በመገኘት ተቃውሞ አሰምተዋል፡፡ ሰኞ ህዳር 15 ቀን 2007 ዓ.ም በድጋሚ በመሰባሰብ 10 ተወካዮቻቸውን ወደ 4 ኪሎ ፓርላማ መላካቸውን በስፍራው የተገኘው የፍኖተ ነፃነት ዘጋቢ አረጋግጧል ፡፡


No comments:

Post a Comment