Thursday, November 27, 2014

በ21ኛው ክ/ዘመን መንግሥት አላባዋ ሀገር ፣መንግሥት አልባው ሕዝብ ።

የኢትዮጵያውያን ደም እንደውሻና እንደ ድመት በአረብ ሀገር አውራ ጎዳና ላይ መፍሰሱ የተለመደ በመሆኑ ዛሬ ዛሬ እንደዜና ለወሬም አልተመቸም አሰልች ሁኗል ።

ትላንት ውባለም የተባለች አንዲት ኢትዮጵያዊት  ቤይሩት ኢጀኑብ (ኢዘሪሂ) በሚባለው ከከተማው ወጣ ባለ አካባቢ ራሷን
ከሶስተኛ ፎቅ ላይ በመጣል ህይወታ ሊያልፍ ችልዋል።

በትላንትናው እለት የ20 አመት እድሜ ያላት ውባለም የተባለች አንዲት ኢትዮጵያዊት የቤት ሰራተኛ በደቡብባዊ ሊባኖን ከአሰሪዎቿ ቤት 2ኛ ፎቅ ላይ ወድቃ ህይወቷ ማለፉ ተነገረ፡፡

አንዳንድ አለምአቀፍ ድርጅቶች የቤት ሰራተኞች ሰብዓዊ መብቶች በስፋት በሚጣስባት ሊባኖን ሰራተኞች ጥቃት እዳይደርስባቸው ለመከላከል እንቅስቃሴ መጀመራቸውን ዴይሊ ስታር ሲዘግብ

በአረብ ሀገራት የሚሰሩ ኢትዮጵያውያን ከፍተኛ ጥቃት የሚደርስባቸው ቢሆንም በየአረብ ሀገራቱ የሚገኙት የኢትዮጵያ ኤምባሲዎች ወይም ቆንፅላ ጽ/ቤቶች ችግሩን ለመቅረፍ የሚያደርጉት ጥረት እንደሌለ አንዳንድ በአረብ ሀገር የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ተናግረዋል፡፡

የዜጎች መብትን ማስጠበቅ ካልተቻለ የኤምባሲዎቹና ቆንፅላ ጽ/ቤቶች እዛ መገኘት ፋይዳው ግልፅ አይደለም ይላሉ ችግሮቹን በቅርበት የሚመለከቱ ኢትዮጵያውያን፡፡


No comments:

Post a Comment