Saturday, August 30, 2014

የመላው ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት (መኢአድ) አመራሮች ታስረው ዋሉ ።

ፖሊስ እና ደህንነቶች የተቃዋሚ አመራሮችን በሰበብ አስባቡ ማንገላታቱን ቀጥሏል።በዛሬው እለት የመኢአድ አመራሮች ታስረው መዋላቸውን የድርጅቱ ምንጮች አስታውቀዋል፡፤ አመራሮቹ ለእስር በማያበቃ እና በፈጠራ ክስ አዲስ አበባ ሰራተኛ ሰፈር መግቢያ ከጣይቱ ሆቴል ፊት ለፊት ካለው የወያኔ ፖሊስ ጣቢያ ከጽ/ቤታቸው ትፈለገላችሁ ተብለው ከተወሰዱ በኋላ ሲያጉሏሏቸው ውለው በዋስ እንደተለቀቁ ተናግረዋል።አመራሮቹ እንደገለጹት ከዚህ ቀደም የአዲስ አበባን ይመኢአድ ቢሮ ማህተሞች እና ሰነዶች ይዞ እንደጠፋ የሚታወቀው መቶ አልቃ ሃይለማርያም የተባለ ግለሰብ ከደህንነቶች ጋር በማበር ወደ ጽ/ቤቱ ፖሊሶችን በማምጣት ‘ወላሞ ‘ብለው ሰድበውኛል የብሄር ብሄረሰብ መብት በተከበረባት ሃገር …ወዘተ በሚል የፈጠራ ክስ ድርጅቱን እና አመራሮቹን ወደ እስር ቤት አስወስዶ ቃል እንዲሰጡ ያደረገ ሲሆን ማስረጃ ባለመገኘቱ ማስረጃ እስኪመጣብሚል ተለቀዋል። ፖሊስ የተቃዋሚ አመራሮችን በማይረባው እና በምማፈለግ አጋጣሚን እየፈለገ ማንገላታቱን ቀጥሏል።

No comments:

Post a Comment