Tuesday, August 12, 2014

ከኢንጂነር ግዛቸው ካቢኔ አምስቱ ራሳቸውን አገለሉ

ኢንጂነግር ግዛቸው በሕዝብ ዘንድ በጉጉት የሚጠበቀዉን፣ ለአገዛዙ ራስ ምታት የሆነው፣ የመኢአድ እና አንድነት ዉህደት አመቻች ኮሚቴን አፈረሱ። በአባላትና ደጋፊዎች ዘንድም ትልቅ ድንጋጤ ተፈጥሩዋል። ከመኢአድ ጎን በመቆም አጋርነት ይገልጻሉ፣ ምርጫ ቦርድ ላይ በጋራ ጫና ለማድረግ ድርጅታቸው ያሰልፋሉ ተብለው የሚጠበቁት፣ ኢንጂነር ግዛቸው፣ ከአንድ ሳምንት በፊት አገር ዉስጥ ላሉ ጋዜጦች የሰጡትን አስተያየት በመቀልበስ፣ የዉህደት አመቻች ኮሚቴዉን ያፈረሱ ሲሆን፣ ለውህደት በሚደረገዉ ከፍተኛ ትንቅን ላይ ቀዝቃዛ ዉሃ ከልብሰዉበታል።
«ኢንጂነር ግዛቸው በአሁኑ ወቅት ከመኢአድ ጋር በመሆን፣ በጋር የሚሊዮኖች ንቅናቄን በማጡዋጣፍ ፣ ሕዝባዊ እንቅስቃሴዎችን በማድረግ፣ በምርጫ ቦርድና አገዛዙ ላይ ጫና ማሳደር ሲገባቸው፣ የዉህደት አመቻች ኮሚቴውን ማፍረሳቸው ሰላማዊ ታጋዮች አንገት የሚያስደፋ ነው» ያሉት በጉዳዩ ላይ ያነጋገርናቸው የፖለቲካ ተንታኝ የኢንጂነሩን ዉሳኔ የሚረዳዉና የሚጠቅመው አገዛዙን ብቻ እንደሆነም ይናገራሉ። በዚህም ያልተደሰቱት የአንድነት አምስቱ አመራሮች

ከኢንጂነሩ ካቤኔ ውስጥ መቀጠላቸው ትርጉመ ቢስ መሆኑን መረዳታቸውን በመግለጽ ለግዛቸው ደብዳቤ ያስገቡት የአንድነት አመራሮች
ተክሌ በቀለ –ተቀዳሚ ምክትል ፕሬዘዳንት
በላይ ፈቃዱ —ምክትል ፕሬዘዳንት
ሰለሞን ስዮም —የፖለቲካ ጉዳዮች ሃላፊ
ዳንኤል ተፈራ — የድርጅት ጉዳይ ሃላፊ
ዳዊት አስራደ —የኢኮኖሚ ጉዳዮች ሀላፊ ::

ፓርቲው በወጣት ተመርቶ ከሌሎች ፓርቲዎች ጋር በመጣመር እና በመተባበር የሚሰራበትን ቀን እንዴት በጉጉት እየጠበቀን እንዳለ ማን ይንገራቸው ??? የፓርቲዉን ሰምም ፣ልፋትም ለማይረባ ስልጣን ብለው ወደህዋላ ባይ ጎትቱት ምን አለ !!!እነዚያ በዓላማቸው ፀነተው በእስር የሚማቅቁት ጀግኖች አያሳዝኑዋቸዉም እንደ ? ወዴት እያመራን ነው? ምነው ኢትዮዽያኖች አንድ መሆን አቃተን ?


No comments:

Post a Comment