Tuesday, August 19, 2014

የትግሉን አቅጣጫ ለማሳት የተላኩ ተኩላዎችን እንጠንቀቅ።

ይህን ሰሞን በአክቲቪስቶች ላይ የሚደረገው ዘመቻ በወያኔው ኢንሳ የተቀናጀ ነው።
በሃገራችን የተንሰራፋውን አምባገንነት ለመዋጋት ባለፉት 20 አመታት አስታውጾ ያበረከቱ በርካታ ኢትዮጵያውያን መኖራቸው የማይካድ ሃቅ ነው። ከሃገር ውስጥ ከተቃዋሚ ፓርቲ አባልነት እስከ በግል ነጻነትንነስከመጠየቅ ለህዝቦች መብት ከመከራከር እስከ አገር መሰደድ የደረሱ በርካታ ኢትዮጵያውያን ዛሬም በየድህረገጹ የራሳቸውን አሊያም አባል የሆኑበትን ድርጅት አስተሳሰብ ጨምሮ በገለልተኝነት መረጃ እና ጹፍ እስከማድረስ የሚሰሩ አክቲቪስቶች ሞልተውናል። የሚያደርሱን መረጃ በትክክለኛው መንገድ ቀን ጠብቆ እውነታው የተረጋገጠ እና እንዲሁም የሚጽፉት ተጽእኖ ፈጣሪነቱ እጅግ የላቀ ነው። ለዚህ ደሞ በፖለቲካ የበሰሉ ሰዎች እና ሃገር ወዳዶች ምስክር ናቸው።

በዚህ ሰሞን ግን እያየን ያለነው አክቲቪስቶችን መወንጀል መፈረጅ ማጣጣል ማዋረድ እጅግ አሳዛኝ ክስተት ነው፡፤ ትላንትና ወያኔን ሲደግፉ የነበሩ እና ለወያኔ ሲቆረቆሩ የነበሩ ጸረ ዲያስፖራ ፔጆች ዛሬን አዛኝ መስለው እንዲሁም በቅርብ ጊዜ ፌስቡክን የተቅላቀል አንዱ ስም ሲነቃባቸው በሌላው እየቀየሩ ህዝብን ለማሳሳት እና የትግሉን አቅጣጫ ለማስቀየስ ደፋ ቀና እያሉ ነው። ለረዥም አመታት ቢያንስ ከ 10 አመት በላይ በየድህረገጹ መረጃ በመስጠት እና ጹሁፎችን በመልቀቅ ታግለው የሚያታግሉ አክቲቪስቶችን አንድ ጊዜ ሙስሊሙን ቢደግፉ ውሃብዬ ግንቦት ሰባትን ብቢእግፉ የቀድሞ ስር አት ናፋቂ ለየት ያለ መረጃ ይዘው ብቅ ቢሉ ወያኔ ወዘተ እየተባሉ ስማቸውን እየጠፋ በዝርክርክ መንፈስ ሃገራችንን እና ትግላችንን ሽንቁር ሊያበጁለት የኢንሳ ተላላኪዎች በርክተው ዘምተዋል።

ስለዚህ ይህን ሰሞን ብአክቲቪስቶች ላይ እየተደረገ ያለው ዘመቻ በወያኔ የደህንነት ተቋም ኢንሳ የተቀናጀ መሆኑን አውቀን ራሳችንን ከነዚህ ትግሉን ለመግደል ከሚራወጡ ተኩላዎች ልንጠብቅ ይገባል ፡፤ ለረዥም ጊዜ መረጅ ብመስጠት እና ጽሁፎችን በመልቀቅ ለህዝብች ልለውን በማስተማር ላይ ያሉ አክቲቪስቶችን በማክበር ለታሪክ ልናቆያቸው ይገባል። ትላንትና በየፌስቡኩ መተው አክቲቪስቶቻችንን በመዝለፍ እና በመፈረጅ ትግሉን ለማስቀየስ የሚሰሩ ተኩላዎች አጃቸውን ከታጋይ አክቲቪስቶች ላይ ሊያነሱ ይገባል።


No comments:

Post a Comment