Friday, August 22, 2014

በባቲ ኦሮሞዎች እና የአጎራባች አፋር ክልል ነዋሪዎች ግጭቱ ተባብሶ መቀጠሉ ተሰማ

ኢሳት ዜና :-በባቲ ወረዳ ልዩ ስሙ ቡርቃ በተባለ ቀበሌ አካባቢ የሚኖሩ የሁለቱ አጎራባች ክልሎች
ነዋሪዎች በተለያዩ ጊዜያት በተኩስ እየተጋጩ በሁለቱም ወገን ሰዎች እየሞቱ ቢሆንም ፤የሁለቱ ክልል መሪዎች ጉዳዩን ለመፍታት ምንም ዓይነት
ጥረት አለማድረጋቸው እንዳሳዘናቸው የባቲ ከተማ ነዋሪዎች ገልጸዋል፡፡
በቡርቃ ቀበሌ የተቀበረ ወርቅ አለ ተብሎ መነገሩ ለግጭቱ መባባስ ምክንያት መሆኑን የሚናገሩት የአይን እማኞች፣ የኦሮምያ ዞን መሬቱን
ለባላሀብቶች ሰጥቶ በማስቆፈርላይእያለበአካባቢውየሚኖሩትየአፋርተወላጆችድርጊቱንበመቃወምበቁፋሮበተሰማሩትሰራተኞችላይተኩስ ከፍተው
ጉዳት ማድረሳቸውን ነዋሪዎች ገልጸዋል።
በተኩስልውውጡምቁጥራቸው በውል ያልታወቀ ሰዎች ከመገደላቸውም በተጨማሪበንብረት ላይ ጉዳት መድረሱን አክለው ተናግረዋል።
አካባቢውን በግል የተደራጁ የአፋር ታጣቂዎች የተቆጣጠሩት ሲሆን የባቲ ወረዳ የፀጥታ ዘርፍ ሃላፊዎች ችግሩን ለመፍታት ቦታውን ከተቆጣጠሩ
ታጣቂዎች ጋር ቢነጋገሩም ታጣቂዎች ማንኛውንም ትእዛዝ ከአፋር መንግስት እስካልመጣ ድረስ አንነጋገር ምበማለታቸው በአጎራባች ክልሎቹ
የጠረፍ ከተሞች መካከል ሊካሄድ የነበረው የሰላም ውይይት በተደጋጋሚከሽፏል።
የሁለቱ ክልል መንግስታት አመራሮች ለጉዳዩ ትኩረት ሰጥተው ለመፍታት ባለመፈለጋቸው ነዋሪዎቹ ወቀሳ አቅርበዋል።
በሁለቱ ክልል ድንበር ያለው ውጥረት ይህን ዜና እስካጠናከርንበት ጊዜ ድረስ እንደቀጠለ መሆኑን የአይን እማኞች ለዘጋቢችን ገልፀዋል፡፡


No comments:

Post a Comment