Thursday, June 12, 2014

በሲኤም ሲ የተደረገው ፍተሻ

ለኢሳት የደረሰው መረጃ እንደሚያመለክተው ፖሊስ በእያንዳንዱ ነዋሪ ቤት እየገባ መታወቂያ የጠየቀ ሲሆን የውጭ አገር ዜጎች ደግሞ ፓስፖርት፣ ወደ አዲስ አበባ የገቡበት ቀን ፣ የቀጣሪ ድርጅታቸውን ስምና አድራሻ፣ መታወቂያና ሌሎችንም ጥያቄዎች ተጠይቀዋል።
ተመሳሳይ ፍተሻዎች በሌሎች አካባቢዎች ሊኖር እንደሚችል መረጃዎች ያመለክታሉ።
በቅርቡ የምእራብ መንግስታት አልሸባብ በኢትዮጵያ የሽብር ጥቃት ሊፈጽም እንደሚችል አስጠንቅቀው ነበር። መንግስትም 2 የአልሸባብ አሸባሪዎችን መያዙን አስታውቋል።
አልሸባብ በሶማሊ ክልል  33 የመንግስትን ወታደሮች መግደሉ ይታወሳል። ይህንን አሰቃቂ ጥቃት ተከትሎ በመንግስትና በአልሸባብ ተዋጊዎች መካከል በተደረገው ጦርነት ከሁለቱም ወገን ከፍተኛ ጉዳት ደርሷል።

No comments:

Post a Comment