Sunday, June 1, 2014

ሰበር ዜና፦

         ከሁለት ወር በፊት ወደ ጣሊያን በመብረር ላይ የነበረ የኢትዬጵያ የመንገድ አውሮፕላን አቅጣጫ በማስቀየር ሲውዘርላንድ ጀኔቭ እንዲያርፍ በማድረግ የጥገኝነት ጥያቄ ኣቅርቦ የነበረው ረዳት ፓይለት ሀይለመድህን አበራ ያቀረበውን የጥገኝነት ጥያቄ የስዊዝ መንግስት ተቀበለ።
       የኢትዮጵያ መንግስት ፓይለቱን ወደ ኢትዮጵያ ለመመስ ሰፊ ጥረት እያደረገ እንደነበር የሚታወስ ሲሆን ፓይለቱ ጥገኝነት እንዲያገኝ በውጪ ያሉ ኢትዮጵያውያን በሰላማዊ ሰልፍ ሲጠይቁ መቆየታቸውም ይታወቃል። ፓይለቱ  በአሁኑ ሰአት በሙሉ ጤንነት ላይም እንደሚገንኝ ለማወቅ ተችሏል በተጨማሪም የፓይለቱ የፍርድ ሂደትም በቅርቡ እንደሚጀምርም ለማወቅ ተችሏል።
       

No comments:

Post a Comment