Monday, May 29, 2017

ለኢትዮጵያ ጉልህ አስተዋጽዖ ያደረጉ ኢትዮጵያውያን ሽልማት ተበረከተላቸው

ኢሳት (ግንቦት 21: 2009)
ለኢትዮጵያ ሃገራቸው ጉልህ አስተዋጽዖ ያደረጉ 8 ታዋቂ ኢትዮጵያውያን መቀመጫውን በዚሁ በአሜሪካ ሃገር ባደረገ ተቋም ሽልማት ተበረከተላቸው።
ማህበረ ጊወራን ዘረ ኢትዮጵያ ወይም /ሲድ/ የተባለው ይኸው ተቋም ላለፉት 25 አመታት ለሃገራቸው ጉልህ አስተዋጽዖ ያደረጉ ኢትዮጵያውያንን በመሸለም ይታወቃል።
በሜሪላንድ ግዛት ኮሌጅ ፓርክ ዕሁድ ግንቦት 20/2019 ከተሸለሙት ስምንቱ ታዋቂ ኢትዮጵያውን መካከል አርቲስት ቴዎድሮስ ካሳሁን እና የትዝታው ንጉስ መሃመድ አህመድ ይገኙበታል።
ሌሎች ተሸላሚዎች ደግሞ ዶ/ር አምባቸው ወሮታ፣ ቻንስለር ለምን ሲሳይ፣ ዶ/ር ዛኪ ሸሪፍ፣ አቶ ቴድ አለማየሁ፣ አባ ከፍያለው አበራ፣ እና ባለፈው አመት ከዚህ አለም በሞት የተለዩት ዶ/ር ማይገነት ሺፈራው ናቸው።

No comments:

Post a Comment