Tuesday, January 3, 2017

የስኳርና የዘይት ዋጋ ጨመረ

በተለያዩ አካባቢዎች የሚደርሱን መረጃዎች እንደሚያመለክቱን የስኳር እና የዘይት ዋጋ ጭማሪ ተደርጎባል።
ገዢው ፓርቲ በሞኖፖል በሚያከፍለው ዘይት ላይ በሊትር 2 ብር ጭማሪ ያደረገ ሲሆን፣ አንድ ሊትር ዘይት በ23 ብር በመሸጥ ላይ ነው። በተመሳሳይ መንገድ በሚከፋፈለው ስኳር ላይም እንዲሁ የ2 ብር ጭማሪ የተደረገ ሲሆን፣ አንድ ኪሎ ስኳር በ23 ብር ተመን እየተሸጠ ነው።
ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የሚታየው የነዳጅ እና የፍጆታ እቃዎች መጨመር፣ በአገሪቱ ከሚታየው የዶላር እጥረት ጋር ሊያያዝ ይችላል ሲል በዘገባው አመልክቷል።

No comments:

Post a Comment