Tuesday, February 17, 2015

የተመላሽ ሰራዊት አባላት የቀረበላቸውን የድጋፍ ጥሪ ወድቅ አደረጉት

የካቲት ፲ (አስር) ቀን፳፻፯ዓ/ምኢሳትዜና :-በኮምቦልቻ ከተማ በቡራሮ አዳራሽ ጥሪ የተደረገላቸው የተመላሽ የመከላከያ ሰራዊት አባላት ለመንግስት ደግፋቸውንና ታማኝነታቸውን እንዲገለጹ በተጠየቁበት ወቅት እስካዘሬ የት እንደወደቅን ሳትጠይቁን፣ አሁን ምን ስለተገኘ ነው በማለት ውድቅ አድርገዋል።
ያለፈው አልፏል ለወደፊቱ እንደጋገፍ በሚል ካድሬዎች የማግባባት ስራ ቢሰሩም ፣ የተመላሽ ሰራዊት አባላት ሳይቀበሉት ቀርተዋል።
አቶ መለስ ጽፈውታል የተባለውን ማንዋል ለማስተማር በሚዘጋጁበት ወቅት ፣ የ ቀድሞ የመከላከያ አባሎቹ በመቃወማቸው ሳይካሄድ ቀርቷል።
መንግስት በተለያዩ ወረዳዎች የሚገኙ ተመላሽ የሰራዊት አባላትን እየጠራ በማነጋገር ላይ ነው


No comments:

Post a Comment