Tuesday, February 3, 2015

የዞን ዘጠኟ ጋዜጠኛ ኤዶም ጸጉሯን ተላጭታ ፍርድ ቤት ቀረበች – “የእምነት ክህደት ቃላችንን ከመስጠታችን በፊት ዳኛው ይነሱልን” – ዞን ዘጠኞች

ጋዜጠኛ ኤዶም ጸጉሯን በመላጨት ኢፍትሃዊነት እና ዘረኝነት መስፋፋቱን በይፋ ተቃውማለች:: – የዞን ዘጠኝ ጦማርያን እና ጋዜጠኞች ዳኛ እንዲቀየርላቸው ማመልከቻ አቅርበዋል:: ምኒልክ ሳልሳዊ እንደዘገበው:- በዛሬው እለት ፍርድ ቤት የቀረቡት ዞን ዘጠኝ ጦማርያን ጋዜጠኞች እንዲሁም የዲብርሃን አዘጋጅ የሆነው ዘላለም ወርቃለማሁ እና ከጋምቤላ በአሸባሪነት የተፈረጁ ኢትዮጵያውያን ይገኙበታል::በኢትዮጵያ የሆላንድ ኤምባሲና ሌሎች ዲፕሎማቶች በፍርድ ቤቱ ጉዳዩን ለመከታተል ተገኝተዋል:: በዛሬው እለት ጋዜጠኛ ኢዶም ጸጉሯን በመላጨት በወያኔ መንግስት እና በእስር ቤቱ ያለውን በፍርድ ቤቱ የሚታየውን አድልዎ የሚደርሰውን ኢፍትሃዊነት እና ዘረኝነት በመቃወም አሳይታለች::


No comments:

Post a Comment