
እንደሆነባቸው የገለጹ ኢትዮጵያውያን፣ በእርግጥም ከነ ድርጅታቸው በሽብርተኝነት የተከሰሱትና የሞት ፍርድ የተላለፈባቸው አቶ አንዳርጋቸው ከእስር ከመፈታታቸውም ባሻገር በቤተመንግስት ከጠቅላይ ሚኒስትሩ ጋር መምከራቸው ፣ መቼም ይሆናል ተብሎ ያልተጠበቀ ተአምር ነው ብለዋል። ከትናንት ምሽት ጀምሮ የኢሳት ዝግጅት ክፍል የስልክ መልዕክት ሳጥኖችም በተመሣሳይ መል ዕክቶች ተጨናንቀዋል። አስተያዬት ሰጭዎቹ በመጨረሻም፣የዶክተር አብይ አህመድ አመራር ከሁሉም ኃይሎች ጋር በጠረጴዛ ዙሪያ በመቀመጥና መሰረታዊ በተባሉ ጉዳዮች ላይ ትኩረት በማድረግ የለውጡን ጅምር ከዳር እንዲያደርሱ ጥሪ አቅርበዋል። የኢትዮጵያ ቴሌቪዥን የፌስቡክ ገጽ የዶክተር አብይን እና የአቶ አንዳርጋቸውን ምስክ ከቨር ፎቶ አድርጎ ሲጠቀም፣ ብአዴን በበኩሉ የዕለቱ ምርጥ ፎቶ የሚል ርዕስ ሰጥቶ በገጹ ላይ ለጥፎታል። ይህ በእንዲህ አንዳለ የአርበኞች ግንቦት 7 ዋና ሰሀፊ አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ ዛሬ ማምሻቸውን ከቦሌ አውሮፕላን ማረፊያ በመነሳት ነገ ጧት ለንደን እንደሚገቡ ታውቋል። በለንደንና አካባቢዋ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን አቶ አንዳርጋቸውን ለመቀበል ዝግጅት እያደረጉ ሲሆን፣ በሌሎች የአውሮፓ ሀገራት ያሉ ደግሞ ጊዜው ስላጠረባቸው ከቀናት በኋላ ሌላ የአቀባበል ዝግጅት እንዲደረግ ጥሪ እያቀረቡ ነው።
No comments:
Post a Comment