በሌላ በኩል የአሜሪካ ድምፅ ያነጋገራቸው በቦታው የነበሩ የዐይን እማኞች ግጭቱ የተጀመረው በበዓሉ መክፈቻ ላይ ንግግር ሊያደርጉ የነበሩ ሰዎች ላያ እና ሊሰቀል በነበረው ባንዲራ ላይ ተቃውሞ በመነሳቱ ነው።
ከግጭቱም በኋላ በርካቶች በተኩስ፣ በአስለቃሽ ጭስ፣ በመረጋገጥ እና ገደል ውስጥ ገብተው ሕይወታቸው እንዳለፈ ተናግረዋ። የተጎዱ ሰዎችን በተመለከተ እስካሁን ይህ ነው የተባለ ትክክለኛ ቁጥር ማግኘት ባይቻልም የዐይን እማኞች ተጎጂዎች 25 በሚሆኑ መኪኖች ሲወሰዱ ተመልክተናል ብለዋል።
የመንግሥት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት በሰጠው መግለጫ፤ “የኢሬቻ በዓልን ባህላዊ አከባበር ጠብቆ ለማክበር የኦሮሞ ህዝብ አባገዳዎችና የኦሮሚያ ክልላዊ መንግስት ያደረጉት ሰፊ ቅድመ ዝግጅት በሁከት ፈጣሪ ኃይሎች ተስተጓጉሏል፡፡ ሁከት ፈጣሪዎቹ ባስነሱት ሁከት በተፈጠረ ግርግር በመረጋገጥ የሰው ህይወት ጠፍቷል፡፡” ብሏል። ዝርዝሩን ከምሽቱ ሦስት ሰዓት ይጠብቁ። (ፎቶ፡ አንዷለም ሲሳይ)
No comments:
Post a Comment